Saturday, March 29, 2014

ኢሕአዴግ ለምን ማኅበረ ቅዱሳንን ማፍረስ ፈለገ?

  • ሥርዐቱ በተለይም መንግሥታዊ ሥልጣናቸውን ለሃይማኖታዊ ተልእኮ የሚጠቀሙ ሓላፊዎችና አማሳኝ የደኅንነት ግለሰቦች አሁን በተያዘው መንገድ ቀጥለው ማኅበረ ቅዱሳንን አላግባብ ወደ መገዳደር ብሎም ከጠቅላይ ቤተ ክህነቱ አማሳኝ ግለሰብ ሓላፊዎች ጋራ ተባብረው ወደ ማፍረስ የሚሸጋገሩ ከኾነ ያለምንም ጥርጥር የተቃውሞው ጎራ ይጠናከራል፡፡ ይህም አገሪቱን በልማታዊ ዴሞክራሲያዊ የአውራ ፓርቲ ሥርዐት ለአርባና ኃምሳ ዓመታት እመራለው ለሚለው ገዥው ፓርቲ ግብዓተ መሬት አፋጣኝ ምክንያት ሊኾን እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች ይስማማሉ፡፡
  • በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ሃይማኖታዊና ምጣኔ ሀብታዊ ፍላጎት ያላቸው የገዥው ፓርቲ ባለሥልጣናትና ጥቂት አማሳኝ የደኅንነቱ ሰዎች ተቋሙን አፍርሶና ቤተ ክርስቲያንን በሒደት አዳክሞ በመቆጣጠር አልያም በታትኖ ለፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ መናፍቃን ማስረከብ ቀላል እንደኾነ ያስባሉ፡፡ በአንጻሩ ‹‹በምድር ላይ ሊሳኩ ከማይችሉ ነገሮች አንዱ ይኼ የአፅራረ ቤተ ክርስቲያን ምኞት ነው፤››የሚለው አንድ የቀድሞው የማኅበሩ ሥራ አመራር አባል እንደሚያሳስበው፣ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያሉ የማኅበሩ አባላትና ደጋፊዎች፣ ማኅበሩ በግቢ ጉባኤያት አንፆ መስቀል በአንገታቸው አስሮ የሸኛቸው በብዙ መቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ምሩቃን፣ ኦርቶዶክሳውያን ምሁራንና በማኅበሩ ስኬታማና ተጨባጭ አገልግሎት የቤተ ክርስቲያን ፍቅር ያደረባቸው ምእመናን ኹሉ ለዘመናት እየመነዘሩ ማንኛውንም የቤተ ክርስቲያኒቱን ተግዳሮቶች የሚመክቱበት መንፈሳዊ ኃይል እንዳላቸው በቅጡ መረዳት ያሻል፡፡
  • በርካታ አገራዊ አጀንዳዎች አሉኝ በማለት ሕዝቡን ለሕዳሴ የሚያነሣሣው መንግሥት፣ በተለይም የፀረ አክራሪነቱን ትግል በቅድመ ግንባር እንዲመራ ፖሊቲካዊ ተልእኮ የተሰጠው አካልና ሓላፊዎቹ፣ መካሪ እንደሌለው የእብድ ሥራ ከመሥራታቸውና እጃቸውን ወደ ብልሽት ከመዘርጋታቸው በፊት ነገሮችን በርጋታ ማጤንና በግልጽ ውይይት ማመን ይበጃቸዋል፡፡
Enqu Magazine Megabit Cover(ዕንቊ፤ ቅጽ ፮ ቁጥር ፻፲፬፤ መጋቢት ፳፻፮ ዓ.ም.)
ከሰሞኑ ኢሕአዴግ መራሹ ግብረ ኃይል ማኅበረ ቅዱሳንን የማፍረስ እንቅስቃሴውን ከየትኛውም ጊዜ በባሰ አጠናከሮ መቀጠሉ እየተደመጠ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሐቀኛና ዓይናማ አበው ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ዘንድ ዐቃቤ ሃይማኖት ኾኖ የሚታየውና በብዙዎች ምሁራን ዘንድ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የምሁራን ክንፍ (academic wing) መኾኑ የሚታመነው ማኅበረ ቅዱሳን የገዥው ፓርቲ ጥቃት ሰላባ መኾኑ አይቀሬነት እውን እየኾነ መምጣቱ ብዙዎችን እያሳሰበ ነው፡፡
በተለይ ጥቃቱ የማኅበሩ የአስተሳሰብ፣ የመርሕና የስትራተጂ ርትዓተ አእምሮ የኾኑ አመራርና አባላቱ ላይ ማነጣጠሩ ርምጃው ደጅ ላይ ስለመኾኑ ማረጋገጫ ተደርጎ እየተወሰደ ነው፡፡ በኢ.ቴቪ ይዘጋጃል ተብሎ የተነገረውም ዶኩመንተሪ የዚሁ ጥቃት መንገድ ጥርጊያ ተደርጐ መታየት አለበት ይላሉ፤ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ምሁር፡፡

የወያኔን ከፋፋይ አገዛዝ እናምክን

የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰብ ሊከበርላቸውና ሊያሳድጋቸው የሚገቡ የተለያዩ የባህልና የታሪክ ቅርሶች ያሏቸውን ያህል በብዙ መንገድ የሚያይዝ የጋራ ታሪክ ቅርስና ዝምድና አላቸው። ልዩነቶቹ ራሳቸው ተጠቃቃሚ ለሆነ የእርስበርስ ግንኙነታቸው ጠቃሚ እንጂ ከአንድ ሀገር ማህበረሰብነታቸውና ከጋራ ህልማቸው ጋር የሚጋጩ የጠብና የግጭት መንስኤዎች አይደሉም። ከጠብና ግጭት ማንኛውም ብሄር ብሄረሰብ ተጠቃሚ አይደለም። ከጠብና ግጭት ጥቅም ይገኛል ብለው የሚያስቡ “ግርግር ለሌባ ይመቻል” የሚለውን የወሮ በላ ፍልስፍና የሚከተሉ የቀን ጅቦች እንጂ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች አይደሉም። በወያኔ የግዛት ዘመን የደረሱትን ግጭቶች መፈናቅሎችና የተፈጠሩትን የእርስበርስ ጥርጣሬዎችን ልብ ብሎ ለተመለከተ ሁሉም በአገዛዙ እና በሎሌ የበታች ሹማምንቱ የተፈጠሩ እንጂ አንድም ጊዜ እንኳን ከህዝብ የመነጩ አይደሉም።
የወያኔ ጉጅሌ በአገዛዝ ዘመኑ ሁሉ ብሄር ብሄረሰቦችን ከሚያይዟቸው የጋራ ማህበራዊ ቅርሶችና ህልሞች ይልቅ ካለመታከት ልዩነቶቻችን ላይ ያተኮረ ፖለቲካ እያካሄደ እንዳለ ግልጽ ነው። ከዚህ አልፎም አዳዲስ የእርስበርስ ግጭቶችን እና ጠቦች እንዲፈጠሩ ተግቶ የሚሰራ ከፋፋይ ቡድን ነው። እርስበርሱ መጠራጠርና መፈራራት እንዲሰፍን ልዩ ልዩ ስልቶችን ይቀይሳል። ከአንዱ ብሄረሰብ ተንኳሽ አዘጋጅቶ ሌላው ብሄረሰብ ላይ አደጋ እንዲደርስ ከዚያም ተጠቃሁ የሚለው አጸፋ እንዲመልስ ያደርጋል። የአንዱን ብሄረሰብ መንደርና ንeበረት በእሳት ለኩሶ በሌላው ብሄረሰብ እንዲመካኝ ያድርጋል። አንዱ በአንዱ ላይ እንዲያማርር ከንፈሩን እንዲነክስ ማድረግ ለወያኔ ጉጅሌዎችና ለሎሌዎቻቸው እንደፖለቲካ ጥበብ ከታየ ሁለት አስርት አመታት አልፈዋል። በየትኛውም የሀገራችን አካባቢዎች የተቀሰቀሱ የርስበርስ ጥርጣሬዎችና ግጭቶችን ያሸተተ ሁሉ ወያኔ፣ ወያኔ እንደሚገሙ ያረጋገጠው ጉዳይ ነው።

የቀድሞው የጋምቤላ ፕሬዚዳንት ደቡብ ሱዳን ከሆቴል ውስጥ ታፈኑ “ወያኔ እጅ ገብተዋል”

የጋምቤላ ክልልን ሲመሩ ቆይተው ባለመስማማት የኮበለሉት የቀድሞው የክልሉ ፕሬዚዳንት ደቡብ ሱዳን ከሆቴል ውስጥ ታፍነው መወሰዳቸው ተጠቆመ። ዜናው በገለልተኛ ወገን ባይገለጽም ኖርዌይ በስደት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩት አቶ ኦኬሎ አኳይ በኢህአዴግ በጥብቅ የሚፈለጉ ሰው ነበሩ።
በመለስ ዜናዊ ውሳኔ በአኙዋክ ተወላጆች ላይ በጅምላ የተከናወነውን ጭፍጨፋ አስመልከቶ ተቃውሞ በማሰማት የኮበለሉት አቶ ኦኬሎ ወደ ደቡብ ሱዳን ከማምራታቸው በፊት ኬንያ እንደነበሩ፣ ከኬንያ ወደ ደቡብ ሱዳን ለምን እንደተጓዙ የዜናው ምንጮች በይፋ ከመናገር ተቆጥበዋል።
ስማቸው እንዲደበቅላቸው የጠየቁ የጋምቤላ አስተዳደር ባልደረባ ለጎልጉል የአካባቢው ዘጋቢ እንደተናገሩት አቶ ኦኬሎ ደቡብ ሱዳን ሆቴል በተቀመጡበት መታፈናቸውን አረጋግጠዋል። “ወያኔ እጅ ገብቷል” ሲሉ ያከሉት እኚሁ ሰው “አቶ ኦኬሎ ብረት በማንሳት ወያኔን ለመታገል ከተነሱ ጋር ተቀላቅለዋል በሚል ስማቸው መመዝገቡንና ወደ ደቡብ ሱዳን ማቅናታቸው በመታወቁ ህወሃቶች እጅ ሊወድቁ ችለዋል” ብለዋል። ምንጩ ይህንን ይበሉ እንጂ አቶ ኦኬሎ አክዋይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያቀኑበትን ምክንያት በርግጠኛነት ሃላፊነት ወስዶ የገለጸ ወገን አልተደመጠም። ኢህአዴግም ቢሆን የቀድሞውን ሹመኛ ስለመያዙ ይፋ ያደረገው ነገር የለም።
ከደቡብ ሱዳን ቀውስ ጋር በተያያዘ የኑዌር ተወላጅ ከሆኑት ሬክ ማቻር ጦር ጋር በመሰለፍ የሳልቫ ኪርን ሃይል ሲወጉ ከተገደሉ ወታደሮች መካከል የኢህአዴግን ሰራዊት መለያ የለበሱ ኑዌሮች መገኘታቸው ውዝግብ አስነስቶ እንደነበር ያመለከቱት ምንጭ “ደቡብ ሱዳን እየወጋት ካለው ኢህአዴግ ጋር አብራ የቀድሞውን የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳደር ከምድሯ ላይ እንዲታፈኑ መፍቀዷ ቅሬታ ያስነሳል” ብለዋል።
ከቤተሰባቸው ተነጥለው በስደት ከሚኖሩበት ኖርዌይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያመሩት የቀድሞው የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳድር ደቡብ ሱዳን በህወሃት ሙሉ ቁጥጥርና ፈቃድ የምትንቀሳቀስ አገር መሆኗን እያወቁ ወደዛ ማቅናታቸውን ባሥልጣኑ “ታላቅ ጥፋት” ብለውታል። ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። በቅርቡ አቶ ኦሞት ኦባንግ መኮብለላቸውና በብዙዎች ዘንድ አውሮጳ እንዳሉ ቢነገርም በትክክል ያሉበት አገር በይፋ አለመታወቁን መዘገባችን ይታወሳል።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Thursday, March 27, 2014

ህወሓት የዘራውን አጨደ

ዛሬ ጠዋት ለህወሓት/ኢህአዴግ የሚያስደስት ለኢትዮጵያውያን ደግሞ መልካም ያልሆነ ዜና ሰማሁ፡፡ አማርኛ እና ኦሮምኛ ተናጋሪ ካድሬዎች ባህር ዳር ላይ በስርዓቱ የተለመዱ አጸያፊ ስድቦችን ተለዋወጡ፡፡ ተደባደቡ፡፡ ይህ እንግዲህ ለኢህአዴግ የዘራውን የጠባብ ብሄርተኝነት እንደማጨድ ይቆጠራል፡፡
የመላው ኢትዮጵያ ጨዋታዎች፣ የብሄር ብሄረሰቦች….ምናምን ተብሎ ከካድሬ ውጭ ማንም ሊገኝ አይችልም፡፡ በዚህ ጨዋታም የተገኙት ሆድ አደር የህወሓት/ኢህአዴግ ካድሬዎች ብቻ ናቸው፡፡ ከወራት በፊት ህወሓት እንደፈለገ የሚጎትተው የብአዴኑ አለምነው መኮንን ወክየዋለሁ የሚለውን ህዝብ አብጠልጥሏል፡፡ እርግጠኛ ነኝ ይህ ህዝብ ‹‹መርዝ›› መሆኑን ለማሳየት ሲባል እራሳቸው እሳቱን ለኩሰውታል፡፡ ደግሞም በአሁኑ ወቅት ህዝብ በሌላ ምሬት ላይ ነው፡፡ ተቃዋሚዎች በስፋት መንቀሳቀስ ጀምረዋል፡፡
ይህን ሁሉ አጀንዳ ሁሌም መሳሪያው ወደሆነው ጎጠኝነት አዞረው፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያንን ሲያደማ ተንፈስ ያለ ይመስለዋል፡፡ ደስም ይለዋል፡፡ ይህ ልክፍቱ ነው! ይህ የባህርዳሩ ግጭት ሆን ተብሎ ታስቦበት የተደረገ የህወሓት/ኢህአዴግ የፕሮጀክት አካል ነው፡፡ ምርጫና ሌላ አስፈሪ ነገር ሲከሰትበት ይህን ካርድ ማውጣቱ የተለመደ ነው፡፡ አዎ! ህወሓት አትርፏል፡፡ ሆድ አደር ካድሬዎች ይህን ፕሮጀክት ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ሊያስፋፉት ይችላሉ፡፡ ታዲያ እነ አለምነውና አባዱላ ምን ስራ አላቸው? እነ አባይ ጸሀዬስ ምን አላማ አላቸው?
Getachew Shiferaw
posted by Aseged Tamene

“ኢህአዴግ ከምሆን ሞቴን እመርጣለሁ” – ኢ/ር ዘለቀ ረዲ (ቃለምልልስ ከሎሚ መጽሔት ጋር)


Zeleke Redi
ኢ/ር ዘለቀ ረዲ ከወራት በፊት በተዋቀረውና አዲስ አመራሮችን በመረጠው አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ውስጥ የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ሆነው መመረጣቸው ይታወቃል፡፡ የሎሚ መፅሔት እውነትን ለህዝብ ለማድረስ ካለባት የሞያ ግዴታ አንፃር በኢ/ር ዘለቀ ዙሪያ በሚነሱ ሀሳቦች ላይ ተንተርሶ የሎሚ ም/አዘጋጅ ቶማስ አያሌው ያደረገውን ቆይታ የመጀመሪያ ክፍል እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ሎሚ፡- አዲሱ የአንድነት ካቢኔ ሥራዎች እንዴት እየተከናወኑ ነው?
ኢ/ር ዘለቀ፡- በጣም ጥሩ ነው፡፡ ኢ/ር ግዛቸው በተለያዩ የአመራር ቦታዎች ላይ አዳዲስ ሰዎችን ነው ያመጣው፡፡ ከዛ አኳያ ጠንካራ ወይም ለቦታው ይመጥናሉ የተባሉ ሠዎች ናቸው የተመረጡት፡፡ ከዚህ ቀደምም ጠንካራ ሠዎች ነበሩ፡፡ አሁን ደግሞ የበለጠ ጠንካራ ሆነው ሊሠሩ የሚችሉ ሠዎች ናቸው የተመረጡት፡፡ እንደሚታወቀው አንድነት መሬት የረገጠ ፓርቲ ነው፡፡ ዝም ብሎ አየር ላይ የተንጠለጠለ ፓርቲ አይደለም፡፡ ከዛ አንፃር ሥራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወኑ ነው፡፡ አሁን ያለው አሠራር በዚሁ ከቀጠለ ጥሩ ውጤት ይመጣል የሚል እምነት አለኝ፡፡
ሎሚ፡- በርካቶች ግን አዲሱን የአንድነት ካቢኔ አወቃቀር አልወደዱትም ይባላል፤
ኢ/ር ዘለቀ፡- ከምን አንፃር?…ግልፅ አድርግልኝ?
ሎሚ፡- አንተን ጨምሮ ሌሎች ሁለት ሶስት ሰዎችን ማካተቱ ትክክል አይደለም የሚሉ ሂሶች ተሰንዝረዋል፡፡ ለምሳሌ፡- አንተን ከፓርቲው ለረጅም ጊዜ ርቆ ነበር፤ ራሱንም ማግለሉንም ተናግሮ ነበር፡፡ ቀደም ሲል በአመራርነት በነበረበት ጊዜ ድክመት ታይቶበት ነበር፡፡ እንደዚህ ዓይነት ችግሮች ያሉበት ሠው እንዴት በአመራር ደረጃ ሊመረጥ ይችላል የሚሉ ወገኖች አሉ፤
ኢ/ር ዘለቀ፡- አንዳንድ ነገሮችን ግልፅ ላድርግልህ፡፡ በመጀመሪያ ከፓርቲው ርቆ ነበር የሚለው ስህተት ነው፡፡ የፓርቲው አባል ነኝ፤ ከፓርቲውም ራሴን አላገለልኩም፤ ከስራ አስፈፃሚነት ራሴን አግልዬ ነበር፤ ከፓርቲው ግን አላገለልኩም፡፡ በብሔራዊ ም/ቤት ውስጥ እሰራ ነበር፡፡ በአባልነትም ቢሆን እሰራ ነበር፡፡ ሁልጊዜ ከፓርቲው ጋር እሰራ እንደነበር ነው የማስበው፡፡ ከፓርቲው ርቆ ፓርቲውን ለቆ ተመልሶ ወደ አንድነት መመለስ ትንሽ ከባድ ነው፡፡ አንድነት እንደ ሌሎች ፓርቲዎች አይደለም፡፡ አንድነት በጣም በነፃነት የሚሰራበት ፓርቲ ነው፡፡ እውነት ነው የምነግርህ፤ እኔ አንድነትን ለማስተዋወቅ አይደለም፡፡ ለምሳሌ ኢ/ር ግዛቸው ዛሬ ተነስቶ እኔ መስራት አይችልም ቢል ለምን የሚል ጥያቄ እንኳን አይቀርብበትም፡፡ እሺ ነው የሚባለው፡፡ ከአንድነት ሥራ አስፈፃሚው እለቃለሁ ሲል ለምን ትለቃለህ ብሎ የሚጠይቅ አልነበረም፡፡ መብትህ ነው፡፡ ማንም ሰው ከአባልነት እለቃለሁ ካለ የመልቀቅ ሙሉ መብት አለው፡፡ እመለሳለሁ ካለም ደግሞ ትቀበለዋለህ፡፡ ከፓርቲው ርቆ የነበረ ሰው ድጋሚ ልመለስ ቢል ትንሽ ከባድ ነው፡፡ አባላቱ ከባድ ናቸው፡፡ ብሔራዊ ም/ቤቱም እንደዚህ እንደምንገምተው አይደለም፡፡
ሎሚ፡- ከዚህ ቀደም ለሰንደቅ ጋዜጣ በሰጠኸው ቃለ ምልልስ ከስራ አስፈፃሚነት በራስህ ፍቃድ መልቀቅህን ተናግረህ ነበር፡፡ የፓርቲው ሊ/መንበር የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ደግሞ አንተን ከቦታው ያነሱት እርሳቸው መሆናቸውን ይናገራሉ፡፡ ይሄን ነገር እንዴት ተመለከትከው?
ኢ/ር ዘለቀ፡- በዚህ ጉዳይ ምንም ባልል ደስ ይለኛል፡፡ ከዚህ ቀደም በእናንተ መፅሔት ላይ እርሳቸው ያሉትን አይቼዋለሁ፡፡ የመፅሔታችሁ ደንበኛ ነኝ፡፡ እርሳቸው እኔ ነኝ ያነሳሁት ብለዋል፡፡ ጥሩ፤ እርሳቸውም ያባሩኝ እኔም ልልቀቅ ችግር የለውም፡፡ አንድነት በነበሩበት ጊዜ ስለሰሩት በጎ ነገር አውርተዋል፡፡ ከበጎ ነገሮች አንዱ ደግሞ እኔን ማባረር ነው፡፡ ከዚህ ላይ ሊያገኙት የሚችሉት ትርፍ ምንድን ነው? እኔን የመሰለ ሠው፣ ራሱን ችሎ የሚንቀሳቀስ፣ የራሱ ሥራ ያለው፣ ፓርቲውን ሊደግፍ የሚችል ሰው ማባረራቸው ነው ውጤታማ ሥራቸው? በጣም በርካታ ሠዎችን አስገብተው እነገሌን አምጥቻቸዋለሁ ማለት ነው የሚሻለው ወይስ ኢ/ር ዘለቀን አባርሬዋለሁ?! እሺ እርሳቸው አባረሩኝ ብዬ ልውሰድ፤ ሰንደቅ ጋዜጣ በገዛ ፈቃዴ መልቀቄን ተከትሎ ጠይቋቸው ነበር፡፡ ያኔ “ኢ/ር ዘለቀ አለቀቀም፤ ሥራ እየሰራ እንደሆነ ነው የምናውቀው፡፡ አልሄደም አለቀቀም” ብለው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በርሳቸው ዕድሜ ያለ ሰው ያንን ምስክርነት መካድ ይችላል?…ያኔ የተናገሩት ነገር መረጃ ነው፡፡ ወደኋላ ተመልሰው እኔን አባረውኝስ ቢሆን? መናገራቸው ምንድነው ትርፉ? እኔና እርሳቸው በዕድሜ በእጥፍ እንለያያለን፡፡ በዕድሜያቸው ብዙ ችሎታ አላቸው፤ ብዙ ለፍተዋል፡፡ ውጤት ማምጣት አለማምጣት የራሱ ጉዳይ ሆኖ ማለት ነው፡፡ እኚህ ሠው እኔ እንኳን በጣም መጥፎ ሠው ሆኜ ባስቸግር እንኳን መልሰው በጣም መጥፎ ሰው ነበር፤ እኔ ነኝ ያስተካከልኩት ቅርጽ ያስያዝኩት ቢሉ ነበር የሚሻለው፡፡ ኢ/ር ዘለቀን ያባረርኩት እኔ ነኝ ማለት ጀብደኝነትም አይደለም፡፡
አንድ ሰው ሊቀ-መንበር የሚሆነው ሰዎችን ለማባረር አይደለም፡፡ ደካማውን ማጠንከር ይጠበቅበታል፡፡ ማንም ሠው ደካማ ሊሆን ይችላል፡፡ እኔ በተፈጥሮዬ ደካማ አይደለሁም፡፡ ደካማ ብሆን ኖሮ አሁን ያለሁበት ቦታ ላይ አልገኝም ነበር፡፡ በትንሹ 150 ሠራተኞችን በስሬ አስተዳድራለሁ፡፡ ከ40 በላይ ቋሚ ሠራተኞች አሉኝ፡፡ ከ200 ሺህ ብር በላይ የወር ደመወዝ እከፍላለሁ፡፡ ይሔን ሁሉ የሚሰራ ሰው ደካማ ነው? ቤተሰቤንም ሆነ ሌሎች ሠዎችን ማስተዳደር የምችል ሠው ነኝ፡፡ ደካማ ብሆንም ከዶ/ር ነጋሶ የምጠብቀው “እንደዚህ ያለ ደካማ ነበር፤ እኔ ነኝ ጠንካራ ያደረግኩት” የሚል ምላሽ ነበር፡፡
ሎሚ፡- የአንድነት የዲሲፕሊን ኮሚቴ ሊቀጣህ የነበረበትና እንዲቀጣህ መመሪያ የተላለፈበት ሁኔታ ነበር?…
ኢ/ር ዘለቀ፡- ዶ/ር ነጋሶ ያላወቁት ነገር ሰው ወንጀለኛ ነው ጥፋተኛ ነው ተብሎ ሊከሰስ እንደሚችል ነው፡፡ አንድ ሌባ ፍርድ ቤት እስከሚፈርድበት ድረስ ተጠረርጣሪ እንጂ ወንጀለኛ አይባልም፡፡ ፍ/ቤቱ ትክክለኛ ውሳኔ እስከሚሰጠው ማለት ነው፡፡ የኔ ጉዳይም በዲሲፕሊን ያስቀጣል አያስቀጣም የሚለውን ማየት የነበረበት የዲሲፕሊን ኮሚቴ ነው አይደል? ያንን ዲሲፕሊን ኮሚቴ ደግሞ ማጠናከር የነበረባቸው ዶ/ር ናጋሶ ናቸው፡፡ እርሳቸው ያዳከሙትንና እርሳቸው የሌላቸውን ዲሲፕሊን ዲሲፕሊን ኮሚቴ ሊሰራው አይችልም፡፡ መጥተው ማቋቋም ይችላሉ፤ በሩ ክፍት ነው፡፡ እመጣለሁ ሲሉ አንድነት ይቀበላል፤ እሄዳለሁ ሲሉ ደህና ሁኑ ይላል፡፡ ጥፋት ኖሮብኝ ቢሆን ኖሮ እቀጣ ነበር፡፡ እርሳቸው ግን ውጭ ሆነው ይቆጫቸዋል፡፡ የኔ አለመቀጣት ትርፉን አላውቀውም፡፡ ፍ/ቤትም አለ እኮ፤ ከዛ ባለፈም እኔን መክሰስ ይቻላል፡፡ እኔ በእውነቱ የዲሲፕሊን ግድፈት አልነበረብኝም፡፡ ም/ቤቱ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ይየው ብሏል አይደል? ይሄ ማለት ደግሞ ዘለቀ የዲሲፕሊን ግድፈት አለበት ማለት አይደለም፡፡ ዲሲፕሊን ኮሚቴውን አጠናክሮ እኔን ወደ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ማቅረብ የነበረባቸው እርሳቸው ነበሩ፡፡ እውነት ለመናገር በእናንተ መፅሔት ላይ እንዳየሁት እኔ በፓርቲ መቀጠሌ ደስተኛ አላደረጋቸውም፡፡ እኔ ለቅቄ እወጣላቸዋለሁ፤ ችግር የለውም፡፡ ውጭ ሆኜ ፓርቲዬን መርዳት እችላለሁ፡፡ ዋናው ግን የሚያገኙት ትርፍ ምንድነው የሚለው ነው፡፡
ከመንግስት በኩል ብዙ ጫና አለብኝ፡፡ የኮንስትራክሽን ድርጅቴ ስምንት ዓመት ሆኖታል፡፡ እስካሁን ድረስ ግን ከመንግስት ሁለት ጊዜ ብቻ ነው የስራ ዕድል ያገኘሁት፡፡ ማንኛውም ኮንትራክተር የኮንደሚኒየም ሥራ የሚሰጠው ተጠርቶ ነው፡፡ የእኔ ድርጅት ግን ኮንዶሚኒየም ላይ አንድ ጠጠር አልጣለም፡፡ ለምን ቢባል ሊያዩኝ ስላልፈለጉ ነው፡፡ የኔ አንድነት ውስጥ መቀጠል ለምን ዶ/ር ነጋሶን ያበሳጫቸዋል? የሶስት ወር ጊዜ ነው የተሰጠን፡፡ አቅም ከሌለኝ የአንድነት ድርጅት አመንክም አላመንክም በሶተኛው ወር ዘለቀ አቅም የለውምና ይውጣ ይላል፡፡ ያንን ጊዜ መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ከኢህአዴግ ጎራ የወጡ ሰዎችን የዲሞክራሲው ትግል አጋር ማድረግ ነበረባቸው፡፡ እንጂ እኔም ላግዝ ብሎ የመጣውን የኔ ዓይነት ሰው አባረርኩት ማለት አይጠበቅባቸውም ነበር፡፡
ሎሚ፡- የአንድነት ፓርቲ የውጪ ግንኙነት ኃላፊ ነህ፡፡ ቦታው ትልቅ ነው፤ ይህንን ትልቅ ቦታ ያገኘኸው ደግሞ ፓርቲያችሁ አንድነት የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት የሚለውን እንቅስቃሴ ባዘጋጀበት ወቅት የገንዘብ ልገሳ ስላደረገ ለውለታው የተሰጠው ነው እንጂ ለቦታው የሚመጥን ሆኖ አይደለም ሲባል ነበር፤
ኢ/ር ዘለቀ፡- በርግጠኝነት ይሄን የሚሉ አዕምሮ ያላቸው ሠዎች ይኖራሉ ብዬ አልገምትም፡፡ ይሄ አንድነትን መናቅ ነው፡፡ አንድነት የት ቦታም እንዳለም አለማወቅ ነው፡፡ እውነቴን ነው የምነግርህ አንድነት ለብር ብሎ በህልውናው ላይ የሚደራደር ፓርቲ አይደለም፡፡ ይሄ የአዕምሮ ማነስም ጭምር ነው፡፡ ይሄ ማለት ዘለቀ አንድነትን በብር ይገዛዋል ብሎ ማሰብ ነው፡፡ አንድነትንም ማናናቅና መወንጀልም ጭምር ነው፡፡ የአንድነት ም/ቤት በሃገር፣ በህዝብ፣ በህልውና ላይ የማይደራደር ም/ቤት ነው፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ሊቀ-መንበር በነበሩበት ጊዜ በአብላጫ ድምፅ የሚወሰነውን ነገር የመስራት ግዴታ አለባቸው አይደል? የራሳቸውን ልዩነት ግን በጋዜጣ ሁሉ ያራግቡ ነበር፡፡ ስለመድረክ ጉዳይ ልዩነት አለኝ ብለው ይፅፋሉ፡፡ ልዩነታቸውን እየፃፉ በአብላጫ ድምፅ ለመገዛት ደግሞ ህጉ ያስገድዳቸው ነበር፡፡ ስለዚህ ዘለቀ ለሚሊዮኖች ድምፅ ገንዘብ ስላወጣ ነው የተመረጠው ብሎ አንድነትን መናገር አሳፋሪ ነው፡፡
ሎሚ፡- ኢ/ር ዘለቀ የኢህአዴግ መልዕክተኛ ነው የሚሉ ወገኖች አሉ፤ ለዚህ አባባላቸው ደግሞ ካሉት ሶስት ም/ጠ/ሚኒስትሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ሙክታር ከድር የቅርብ ወዳጅና ከወዳጅነትም በላይ በአንድነት ውስጥ የማዳከምና የአንድነትን እቅስቃሴ ለመቅጨት ሰርጎ እንዲገባ የተደረገ መልዕክተኛ ነው ይባላል፡፡ አንተስ ሰምተሃል? ምንስ ትላለህ?

የጫፌ ኦሮምያ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ



መጋቢት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጨፌ ኦሮምያ ትናንት የጀመረውን የምክር ቤቱን መደበኛ ስብሰባ ሲያጠናቀቅ ምክትል ጠ/ሚኒስትር እና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒሰትር የሆኑትን አቶ ሙክታር ከድርን በፕሬዚዳንትነት፣ እንዲሁም አቶ ለማ መገርሳን በአፈ ጉባኤነት መርጧል።
ምንም አይነት ተወዳዳሪ እጩ ባልቀረበበት የድጋፍም ሆነ የተቃውሞ ድምጽ ሳይሰማ ፕሬዚዳንቱም አፈ ጉባኤውም ተመርጠዋል።
ሌሎች የምክር ቤት አባላት አፈ ጉባኤው የፕሬዚዳንቱን ስም ጠርተው እንዲያጸድቁ እስከሚጠይቁዋቸው ድረስ የእጩዎችን ስም እንኳ እንደማያዉቁ ሂደቱን የተከታተለው ዘጋቢያችን ገልጿል።
ካፒታል የተባለው በአገር ውስጥ የሚታተመው የእንግሊዝኛ ጋዜጣ የኦፒዲዮ ምክትል ሊቀመንበር ወ/ሮ አስቴር ማሞ ይሾማሉ ሲል በሰበር ዜና ዘገባ ማቅረቡ ይታወሳል።
ኢሳት በትናንት ዘገባው ወ/ሮ አስቴር ማሞ የክልሉ ምክር ቤት አባል አለመሆናቸውን በመግለጽ ዘግቦ ነበር። ጉዳዩን በቅርብ ከሚከታተሉ ሰዎች ለመረዳት እንደተቻለው ወ/ሮ አስቴር ከፍተኛ የሆነ የጤና ችግር አለባቸው።

የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ቀጣይ የተቃውሞ መርሃግብር



መጋቢት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ላለፉት 2 አመታት ሲካሄድ የቆየው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጋብ ብሎ የነበረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ አርብ እንደሚጀመር ታውቋል። የተቃውሞ መሪ መፈክሩ “ሰላታችንን በመስኪዳችን” የሚል እንደሆነና መስኪዶችን በመንግስት ታማኞች ለማስያዝ የሚደረገውን እንቅስቃሴ ለመቃወም አላማ ያደረገ ነው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የድምጻችን ይሰማ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የፍርድ ሂደት ዛሬ ተጀምሯል። ተከሳሾቹ የመከላከያ ምስክሮቻቸውን ለማሰማት በተገኙበት ወቅት የማህልና የቀኝ ዳኞች ተቀይረው በአዲስ ተተክተው አግኝተዋቸዋል።
የአለማቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች በሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ የሚካሄደው የፍርድ ሂደት ፖለቲካዊ ይዘት ያለውና ነጻ አይደለም በማለት ውድቅ ማድረጋቸው ይታወቃል።

“ለውጡ እንደቀረበ ጥርጥር የለኝም” ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር

ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ከሁለት ወር በፊት ወደ አሜሪካና የአውሮፓ አገራት ለስራ ጉብኝት ሄደው ነበር፡፡ አሁንም ወደ አሜሪካ ጉዞ ሊያደርጉ እንደሆነ ሰምቻለሁ፡፡ የአሁኑ ጉዞ አላማ ምንድን ነው?
Eng. Yilkal Getnet Semayawi party chairman with Negere Ethiopia newspaper
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር
ኢንጅነር ይልቃል፡- መጀመሪያ ያደረኩት ጉዞ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የፓርቲውን አላማና ፕሮግራም፣ የሰራናቸውን እንዲሁም ወደፊት ልንሰራቸው ያሰብናቸውን ስራዎች፤ ሰማያዊ እንደ አዲስ ኃይል ሲመጣ የቆመላቸው ሀሳቦችና እምነቶች ምን እንደሆኑ ለማስተዋወቅ ታስቦ የተደረገ ነበር፡፡ የአሁኑ ግን ከበፊቱ የተለየና ለሰማያዊ ሊቀመንበር በሚል በቀጥታ በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት የተደረገ ግብዣ ነው፡ ፡ የአሁኑ ወጣት የአፍሪካ መሪና ወደፊትም ለአገራቸው መሪ ሊሆኑ የሚችሉ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ጥሩ ስራ የሰሩ፣ በውድድር ከተመረጡ በኋላ በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት በሚደረግ ምርጫ መመዘኛዎቹን ለሚያሟሉ ሰዎች የሚሰጥ እድል ነው፡፡ በመመዘኛዎቹ መሰረት በማሸነፌ የአሜሪካ መንግስት ሙሉውን ወጭ ሸፍኖ ለሶስት ሳምንት በአሜሪካ የመንግስት አወቃቀርና ዴሞክራሲን ጨምሮ በተግባር የሚሰጡ ስልጠናዎችን የማግኘትና፣ የአሜሪካ መንግስት ባለስልጣናትም ባሉበት ከተለያዩ ተቋማት ጋርም ለመገናኘት እድል ይኖረኛል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ከሌሎች የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ መሪዎች ጋር ተወዳድረው ነው ያሸነፉት ማለት ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- አዎ! ግን ሌሎች ያሸነፉ ተጨማሪ ሰዎች ይኑሩ አይኑሩ አላውቅም፡፡ ይህ የፕሬዝዳንቱም ‹ኢኒሸቲቭ› ይመስለኛል፡፡ ለእኔ ግን የተሰጠኝ አዲስ ትውልድ አመራሮች፣ ወደፊትም በአገራቸው መሪ መሆን የሚችሉ፣ ስትራቴጅካሊ የሚያስቡ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይም ሆነው መልካም ስራ ለሰሩ ሰዎች የሚሰጥ ልዩ የጉብኝት እድል ነው፡፡ በአጠቃላይ ውድድርም ተደርጎ የሚወሰድ ነው ማለት ይቻላል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የአሜሪካ መንግስት ይህንን እድል ሲሰጥ እርስዎ እንደ መሪም ሆነ ሰማያዊ እንደ ፓርቲ ያሸነፋችሁበትን ዋና ዋና መመዘኛዎች ነግረዋችኋል?
ኢንጅነር ይልቃል፡- ሲመርጡኝ ዝርዝር መረጃዎችን ወስደዋል፡ ፡ መሰረታዊ የሚባሉትን ለምሳሌ ያህል የፖለቲካ ቆይታዬ፣ የትምህርት ዝግጅቴን፣ በፖለቲካው ውስጥ የነበረኝን ተሳትፎ የመሳሰሉትን መረጃዎች ለእጩነት በቀረብኩበት ወቅት ከእኔ ወስደዋል፡፡ ከዛ በኋላ ያስመረጠኝን ዝርዝር መስፈርት አላውቅም፡፡ ነገር ግን ወጣት (እስከ 45 አመት ባለው ውስጥ)፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ መልካም ስራ የሰራ፣ ወደፊትም የአገሩ መሪ ሊሆን የሚችል የሚሉት ዋና ዋና መመዘኛዎች እንደሆኑ አውቃለሁ፡ ፡ ይህም በተለይ ከሰማያዊ አንጻር ከሁለት ነገሮች አኳያ እንድናየው ያደርጋል፡፡ አንደኛው በምስራቅ አፍሪካ ያለውን ፖለቲካና እስካሁን ጠቅልሎ የያዘው ኢህአዴግ ነበር፡፡ ሌላ አማራጭ እንደሌለ አድርጎ ነበር የሚያየው፡፡ ሆኖም እንደዚህ አይነት እድል እንደ አሜሪካ ባለ ትልቅ መንግስት የተቃዋሚ መሪ የተለየ ስራ ሰርቷል ተብሎ ሲጋበዝ ሰማያዊ ፓርቲ አዲሱንና ወደ ፖለቲካ ያልመጣውን ትውልድ ወደ ፖለቲካው ለማምጣት በሚያደርገው ጥረት እንደ አንድ ማበረታቻ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ይህ በሌሎች መስኮች ከምናደርጋቸው የዲፕሎማሲ ስራዎች በተጨማሪ ለሰማያዊ ፓርቲ ከሌሎች ፓርቲዎች በተለየ ይህኛው ግብዣ ሲደረግለት ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡
ከአሁን በፊት ለሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በአሜሪካ ኤምባሲ ውስጥ የ35 አገራት ኤምባሲዎች የ‹ኢትዮጵያ ፓርትነርስ ግሩፕ› የሚባለው ሲደረግ በአመታዊ ስብሰባቸው ላይ ዋና ተናጋሪ ሆኜ ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካና ስለ ሰማያዊ ፓርቲ ዋና የትግል እንቅስቃሴና የወደፊት አላማችን እንዳስረዳ የተለየ እድል ተሰጥቶኛል፡፡ ይህም ለፓርቲው ሌት ተቀን ለሚሰሩ ወጣቶች፣ እንዲሁም ሁል ጊዜም ቢሆን ወጣቱ ተከታይና ጀሌ እግረኛ ከመሆን አልፎ ራሱ ኃላፊነት የሚወስድ፣ መምራትና የራሱን መሪዎች ማውጣት የሚችል ትውልድ መምጣቱን የሚያሳይ መልካም ጅምር ነው፡፡

Sunday, March 23, 2014

ሃያ ሦስት የስቃይ፤ የሰቆቃና የእልቂትና ዓመታት

የኢትዮጵያ ህዝብ በፋሽስቱ ህወሓት ብልሹ አስተዳደርና አምባገነናዊ አገዛዝ ስር ወድቆ በኑሮ ውድነትና በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ፣ ሰብኣዊና ዲሞክራሲያዊ መብቱ ተነጥቆ ለአፈናና ለእስራት እየተዳረገ፣ ሉዓላዊ ክብሩ ተደፍሮ ለም መሬቱንና አንጡራ ሃብቱን እየተሸነሸነና እየተቦረቦረ ለባዕድ እየተሸጠ፣ በገዛ ሀገሩ ተፈናቃይና የውጭ እጅ ተመልካች ሆኖ ለስደትና ለእንግልት እየተዳረገ እነሆ ዛሬ ከ23 ዓመት በላይ የሰቆቃ፣ የእልቂትና የመከራ ዓመታት ተቆጠሩ።
ለአለፉት 23 ዓመታት የደፈረሰው ፖለቲካችን ወደ ጭቃነት እየተቀየረ ስለመሆኑም ምንም ምስክር አያሻውም።ፋሽስቱ ወያኔ ከሀገር ሉዓላዊነት እስከ ታሪካችን፣ ከባንዲራችን እስከ እንደ ሕዝብና እንደ ሀገር ያለን ደረጃ መቀመቅ አውርዶታል። አንዳንዶቻችን እንደዚህ ዘመን ትውልድ አባልነታችን ያለፈውን መለወጥ፣ ዛሬን የሰውነት ደረጀችን በጠበቀ ሁኔታ መኖርና ነገንም ላልተወለዱ ልጆቻችን መልክ አስይዞ ለማውረስ ከቁጥጥራችን እየወጣ መሆኑን በግልጽ እንመለከታለን። በሌላ ወገን ወያኔዎቹ የአለፉት 23 ዓመታት የአንድ ጀምበር ያህል አጥረውባቸው፤ ተጨማሪ 40 አመታትን ለመግዛት በማለም ሲንፈራገጡና በቀቢጸ ተስፋ ህዝብን ለማማለል ሲሞክሩ እያየንና እየሰማን ነው። ስንራብ መጥገባችንን ይነግሩናል። ስንታረዝ ደራርበን መጎናፀፋችን ይታያቸዋል። ሀገራችን ከአለም ሀገሮች ተርታ በሁሉም መስኮች ለማለት በሚያስደፍር ደረጃ በማይታመን ፍጥነት እየወጣች ወደ ግርጌ ስትወረወር፤ ወንበዴዎቹ ወያኔወች ግን ሀገራችን ተሞሸረች አማራች ይሉናል። የኢትዮጵያን ሕዝብ ሲረግጡት የሚደቅን ቅጠል ያህል በመቁጠር ከህግና ከአመክንዮ ውጭ በማን አለብኝነት ሕዝባችንን በንግድ ድርጅቶቻቸው እየገፈፉ እርቃኑን አስቀርተውታል።
ጉጅሌው ወያኔ ሥልጣን ሲይዝ፣ ከፎከረባቸው አንዱ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በቀን ሶስቴ የሚበላበትን ሁኔት ፈጥሮ ከረሀብ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚገላገልበትን ባዶ ቃል ኪዳን ገብቶ ነበር። ነገር ግን ዛሬ የኢትዮጵያ ሕዝብ በቀን ሶስቴ አበሳውን እየበላ ይገኛል። ምግብማ ከየት ተገኝቶ! ረሀቡ፣ ጠኔው ከዛሬ ሀያ ዓመት ሁኔታ በሶስት ዕጥፍ ጨምሮ፣ ዛሬ እስከ 25 ሚሊዮን ሕዝብ ጦሙን የሚያድርባት አገር ስለሆነች በየጊዜው የተባበሩት መንግስታትና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ከሚያወጡት መግለጫ መረዳት ይቻላል። ዛሬማ፣ ነጻ ገበያ ብሎ የፎከረብን ነጻነት ተረስቶ የዘይትና የስኳር ዋጋ እስከመቆጣጠር ገብቷል። ከመብራት፣ ውሃና ኔትዎርክም ብሶ ህዝብ በእጦት ከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ይገኛል። በቅርቡም በመላ ሃገሪቱ መብራት፣ ውሃና ኔትዎርክ እጦትን አስመልክቶ ሰልፍ ሊወጣ ቅድመ ዝግጅቶች እየተገባደዱ እንደሆነም እየተሰማ ነው። ከዚህ በላይ የጨለማ ጊዜ የለም።
የወያኔ አገዛዝ ለአለፉት 23 ዓመታት የሀገሪቱን ብሄራዊ ጥቅም አሳልፎ በመስጠትም በተደጋጋሚ ብሄራዊ ክህደት ሲፈጽም የቆየ ቡድን ነው። ይህንን ብሄራዊ ክህደት ሲፈጽም ካለማወቅ፤ ከችኮላ ወይም በደመነፍስ ከመጓዝ የተሠራ ስህተት አይደለም። ከአጠቃላይ የፓለቲካ ስትራተጂውና ግብ ጋር የተያያዘ አካሄድ ስለመሆኑ መስካሪ አያሻም። ፋሽስቱ ህወሓት በህዝብ የተተፋ ቡድን በመሆኑ የሀገሪቱን ፓለቲካና ኤኮኖሚ ለመቆጣጠር የውጭ ኃይሎችን የገንዘብ፤ የወታደራዊና የዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ ስለሚሻ ነው የሀገሪቷን ብሄራዊ ጥቅሞች መረን በለቀቀና ድፍረት በተሞላበት መልክ ለውጭ ኃይሎች በየጊዜው አሳልፎ የሚሰጠው።ለዚህም ነው የምግብ እጥረት ያለባት የሀገራችንን ሰፋፊ ድንግል መሬቶቿን ለሀገሪቷ ዜጎች ከልክሎና አፈናቅሎ ለመካከለኛው ምሥራቅና ለእስያ ሀገሮች ልማታዊ ድርጅቶች በነፃ በሚባል ደረጃ እስከ 99 ዓመት በሚደርስ ውል ፈርሞ እየሸጠ የሚገኘው። ሰፊ ለም የድንበር መሬታችንንም ቆርሶ ለባዕዳን በመሸጥ ላይም ለመሆኑ ከሰሞኑ ለሱዳን ተላልፎ የተሰጠው መሬት ማስረጃ ነው።

Thursday, March 20, 2014

አዲስ አበባ “ለእሪታ ቀን” እንድትዘጋጅ ተጠየቀ! “ኢህአዴግ አገር የመምራት ብቃት እንደሌለው አዲስ አበባ ማሳያ ናት!!” | Zehabesha Amharic

አዲስ አበባ “ለእሪታ ቀን” እንድትዘጋጅ ተጠየቀ! “ኢህአዴግ አገር የመምራት ብቃት እንደሌለው አዲስ አበባ ማሳያ ናት!!” | Zehabesha Amharic

የኢትዮጵያ ተተኪ ሴቶች ትውልድ መነሳሳት!

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

“ከዚህ በኋላ ትዕግስታችን ተሟጧል!”

ሰማያዊ ፓርቲ በኢትዮጵያ እንደገና ወኔ የተሞላበት የትግል መንፈሱን በማደስ ጥንካሬውን አሳየ !
Semayawi party female youth activists released
እ.ኤ.አ ማርች 9/2014 የተከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች በዓል ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ ተዘጋጀቶ በነበረው የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶችም ተሳትፎ አድርገው ነበር፡፡ ከዴሞክራሲያዊ ምርጫ ባፈነገጠ መልኩ በኃይል በስልጣን ኮርቻ ላይ ተፈናጥጠው ስልጣንን የሙጥኝ በማለት ከህግ አግባብ ውጭ በህዝብ ላይ ደባ በመፈጸም ላይ የሚገኙትን የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች ዕኩይ ምግባር የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲገነዘበው በማሰብ ወጣት ሴቶቹ እውነታውን ያለምንም መሸፋፈን በማጋለጥ እምቢ አሻፈረኝ በማለት ተቃውሟቸውን ለዓለም በይፋ አሰምተዋል፡፡ እንዲህ በማለትም ተቃውሟቸውን አጠናክረዋል፣
“ከዚህ በኋላ ትዕግስታችን ተሟጧል! ተርበናል! ነጻነት እንፈልጋለን! ነጻነት እንፈልጋለነ! እስክንድር ይፈታ! አንዷለም ይፈታ! አቡባከር ይፈታ! ርዕዮት ትፈታ! የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ ይፈቱ! ፍትህ እንፈልጋለን! ነጻነት! ነጻነት! ነጻነት! አትከፋፍሉን! ኢትዮጵያ አንድ ነች! አንድ ኢትዮጵያ! ከዚህ በኋላ ትዕግስታችን ተሟጧል! ውኃ ናፈቀን! መብራት ናፈቀን! ተርበናል!…“

Wednesday, March 19, 2014

የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች በዋስ ተፈቱ

መጋቢት ፲ (አስር) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 10 የፓርቲው ሴት እና ወንድ አመራሮች ያለፉትን 11 ቀናት በእስር ቤት ካሳለፉ በሁዋላ ፖሊስ እያንዳንዳቸውን በ3 ሺ ብር ዋስ ለቋቸዋል። ምንም እንኳ አቃቢ ህግ ክስ ለመመስረት የሚያስችል በቂ ማስረጃ የለኝም ቢልም፣ ፖሊስ እስረኞችን በነጻ ከመልቀቅ በዋስ መልቀቅን መርጧል። የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃ እንደሚሉት እስረኞቹ በነጻ ካልሆነ በዋስ አንፈታም የሚል አቋም ቢይዙም፣ የፍትህ ስርአቱን መበላሸት እስካሳዩ ድረስ ትግሉን ለመቀጠል ሲባል በዋስ እንዲፈቱ ለማግባባት ተሞክሮ መፈታታቸውን ገልጸዋል
የእስር ቤት አያያዛቸውን በተመለከተ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆነው ወጣት ብርሃኑ ተክለያሬድ ከኢሳት ጋር ያደረገውን አጭር ቆይታ ከዜናው መጨረሻ የምናቀርብ መሆናችንን እንገልጻለን

ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ስነምግባር ደንብ እንደማይፈርም አስታወቀ | Zehabesha Amharic

ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ስነምግባር ደንብ እንደማይፈርም አስታወቀ | Zehabesha Amharic

አባ መላ ሳይበላ ተበላ !

ሆዳም! ስለሚበላው እንጂ ስለሚባለው አይጨነቅም!

አዜብ ጌታቸው
አባ መላ ነኝ የሚለው የፓልቶኩ ብርሃኑ ዳምጤ ሰሞኑን የሰራው ስራ ከማንም በላይ የጎዳው እራሱን ነው።  ከአንድ ድርጅት ውልቅ ብለው በዚያው ጀንበር ሌላው ድርጅት ጥልቅ የሚሉ፤ ያም ሳይጥማቸው ወይም ሳይመቻቸው ይቀርና ወዲያው ደሞ ወደ ሌላ 3ኛ 4ኛ….. ድርጅት ጥልቅ ውልቅ የሚሉ ጥቂት የማይባሉ ቅብዝብዞችን አውቃለሁ።እነኚህ አይነቶቹ የቻሉትን ያህል እንደ ፌንጣ ዘለው ዘለው በመጨረሻ እዩኝ እዩኝ ያለ ……እንዲሉ፦ ራስን ብቻ አባል በሚያደርገው ዲፕሬሽን ወደ ተሰኘው ድርጅት ይገቡና ፍጻሜያቸውም እዛው ይሆናል።
ሰሞኑን በአባ መላ የታየው ዝላይ ግን በፌንጣ ተምሳሌት ከተገለጹት ቅብዝብዞች የተለየ ነው፡፡ አባ መላ ውልቅ ካለበት የወያኔ ጓዳ ያሞሌ ተመኑን ቀንሶ ዳግም ጥልቅ ብሏል። ስለዚህ ለአባ መላ ተግባር በተምሳሌነት የምትጠቀሰው ፌንጣ ሳትሆን የተፋውን መልሶ የሚውጠው ጉማሬ ይመስለኛል ።
ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድህን ወያኔን ጉማሬ ብለው የገለጹበትም ምክንያት ይህው ነበር፡፤ በነገራችን ላይ ብርሃኑ ዳምጤ በአንድ ቃለ ምልልስ ላይ “አባ መላ” የሚለውን ቅጽል ያወጡለት ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድህን መሆናቸውn (he was my best friend) አይነት ድምጸት) ሲናገር ሰምቸዋለሁ፡፤ የሞተ አይጠይቅ ሆነና ዝም ብለን ሰማነው።
ይሁን እንጂ በበኩሌ እንደሚታየኝ ብርሃኑ ዳምጤ የተሰ|ኘ የተሰፋ ሙዝ የሚሸጥ የምናለሽ ተራ ቁጭ ይበሉ (ምንጭ አብሮ አደጉ)ና የብርቅየውን ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬን ጓደኝነት እንኳን በዕውን በልቦለድ ድርሰትም ቢካተት ለአንባቢ የሚጥም አይመስለኝም፡፤  ልቦለድም ቢሆን እኮ የገሃዱ ዓለም እንጂ የከሃዲው አለም ነጸብራቅ  ነው አልተባለም።….
ወደ ቀምነገሩ ልመለስ፦ አዎ ብርሃኑ ዳምጤ እነ ሎሬት ጸጋዬን እየጠቃቀሰ ፕሮፊይሉን ከፍ ከፍ እያደረገ ቢቆይም ሰሞኑን በሰራው ታሪካዊ ክህደት ያበገነው አብሮ አደጉ ያለ ከፈን ምናለሽ ተራ ቀብሮታል።
ለዚህም ነው ብርሃኑ በሰሞኑ ተግባሩ ከማንም በላይ የጎዳው ራሱን ነው ያልኩት፡፤
ከልብ አጢናችሁት ከሆነ የብርሃኑ ዳምጤ ችግር “ሞራል አልባ” መሆኑ ነው። ሞራል አልባ ሰዎች የሌላውንም ሞራል ለመጨፍለቅ ሁለቴ ማሰብ አያስፈልጋቸውም። ሞራል አልባ ሰዎች ፤ ምን ይሉኝ? አይሉም።ምን ይሉኝ የሚለውን ጥያቄ በአግባቡና በቦታው ማንሳት፤ የሞራል ድቀት ከሚያስከትል አደጋ ያድናል። ብርሃኑ ዳምጤን መሰል ሰዎች ይህን ጥያቄ አያውቁትም።
ለዚህም ነው ትናትና እንኳን ለተሰዳቢው ለሰሚው በሚዘገንን ጸያፍ ስድብ ያበሻቀጣቸውን የወያኔ ባለስልጣናት  ዛሬ  “ማሪኝ ብዬሻለሁ” እያዜመ የሚለማመጠው።
ግን ለምን?
ጥሩ ጥያቄ ነው…ሞራል አልባ ሰው የማንነቱ ነገር ብዙም አያስጨንቀውም። ተደፈረብኝ። ተገሰሰብኝ የሚለው እሱነት የለውም። ስለሚበላው እንጂ ስለሚባለው አይጨነቅም። ለሱ ማንነት? ከሚለው “የስብዕና” ጥያቄ ይልቅ ምቾት፤ ድሎት፤ ቅንጦት፤…..የተመቸ ህይወት ቅድሚያ አላቸው። በአጭሩ ሞራል አልባ ሰዎች ከምንም ከምንም ይልቅ ለሆዳቸው ቅድሚያ ይሰጣሉ።ብርሃኑ ዳምጤም ያደረገው ይህንኑ ነው።
ከወያኔ ኩብለላ
የወያኔ ባለ ስልጣናት የአውራቸውን ሞት ተከትሎ በራሳቸው የውስጥ ችግር ተንጠው፤ ውጭ ለታሰሩት ውሾች ይሰ|ጡ የነበሩትን መደበኛ መሽሩፍ አቋረጡ። በዚህ ምክንያት አለን ከሚሏቸው ተናካሽ ውሾቻቸው አንዱ (አባ መላ) ሰንሰለቱን በጥሶ ወደ ተቃዋሚው ጎራ ተቀላቀለ።

በተቃዋሚው ጎራ ቆይታ፦
ሰንሰለቱን በጥሶ የመጣው አባ መላ አክቲቪስት ተባለና(ይታያችሁ ሞራል አልባ ሰው የሰባዊ መብት ተሟጋች ሲሆን)  የድሮ ጌቶቹን አብጠለጠለልን። ሙታንታ ማድረግ የማያውቁ ፍልጦች የሚል ኢ.ሞራላዊ ስድብ አወረደባቸው። እግረ መንገዱንም ሙታንታን ያህል የግል ገበና ሁሉ አውቃለሁ አይነት ራሱን አካበደ።