ቅዳሜ ዕለት የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ዛሬ ከሰአት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡
ቅዳሜ እለት በጃንሜዳ ፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ ታስረው የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ችሎት አካባቢ ወደሚገኘው ወረዳ 9 ፖሊሰ ጣቢያ ተወስደው 2 ቀን እንዲያድሩ ከተደረጉ በኋላ ዛሬ ጠዋት ወደ ጃንሜዳ ፖሊስ ጣበያ ተመልሰው የተወሰዱ ሲሆን አሁንም በጃንሜዳ ፖሊስ ጣቢያ ይገኛሉ፡፡ በወረዳ 9 የ2 ቀን ቆይታቸውም የፖሊስ አባላት በግዴታ የወንዶቹን ፀጉር የቆረጧቸው መሆኑ ተረጋግጧል፡፡አባላቱ ዛሬ በ8 ሰአት ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ የተነገራቸው ሲሆን በጃንሜዳ ፖሊስ ጣቢያ የፓርቲው አባላትና ከፍተኛ አመራሮች እየጠየቋቸው ይገኛሉ፡፡
No comments:
Post a Comment