Tuesday, October 14, 2014

(ሰበር ዜና) ለ1ዓመት ከ6 ወር በላይ በእስር ሲሰቃዩ የቆዩት 12 ተማሪዎች እና 1 መምህር የ6 ወር እስራት ተፈረደባቸው

በእስር የቆዩበት ጊዜ ከተፈረደባቸው በመብለጡ ከእስር እንደሚፈቱ ተወስኗል!

ማክሰኞ ጥቅምት 4/2007


(ድምፃችን ይሰማ እንደዘገበው፡) ከ21 ወራት በፊት ከጅግጅጋ፣ ከሲቪል ሰርቪስ፣ ከባህር ዳር፣ ከጅማ፣ ከደሴ፣
ከሐዋሳና ከደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲዎች ታፍነው የታሰሩ 12 ሙስሊም ተማሪዎችና 1 አስተማሪ የስድስት ወር የእስር
ቅጣት ተበየነባቸው! በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ወንጀል ሕግ አንቀጽ 32/1/ሀ፣ አንቀጽ 38/1፣ እንዲሁም አንቀጽ 257/ሀ
ላይ በሰፈሩት አንቀጾች መሰረትነት የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ሃይማኖታዊ ስነስርአትና አለባበስን በሚመለከት ያወጣውን
የስነምግባር ደንብ በመቃወም የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመፍጠር ‹‹በመላው አገሪቱ አመጽ በመቀስቀስ በሃይማኖት
ሽፋን በአገሪቱ ያለውን ሰላም ማወክ›› እና ‹‹የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎቹን በኃይል ለማስፈታት በመጣር›› የሚሉ
ክሶች ተመስርተውባቸው ክሳቸው በልደታ ፍርድ ቤት ከ18 ወራት በላይ ሲታይ የዘለቀው ተማሪዎች ዛሬ የመጨረሻ ብይን
በፍርድ ቤቱ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

(ሰበር ዜና) ለ1ዓመት ከ6 ወር በላይ በእስር ሲሰቃዩ የቆዩት 12 ተማሪዎች እና 1 መምህር የ6 ወር እስራት ተፈረደባቸው

መንግስት የበረታበትን የህብረተሰቡን ተቃውሞ ‹‹አስተነፍሳለሁ›› በሚል ዓላማ ከጥር 2005 ጀምሮ ከሚማሩባቸው
የተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች አፍሶ ለእስር የዳረጋቸው እነዚሁ ተማሪዎች ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ መስከረም 27/2007
በፍርድ ቤቱ የጥፋተኝት ውሳኔ የተሰጠባቸው ሲሆን የቅጣት ብይን ለመስጠት ለዛሬ ቀጠሮ ያስቀመጠው ፍርድ ቤትም
የስድስት ወራት እስርና ምክር እንዲሰጣቸው ወስኗል፡፡ በሃያዎቹ እድሜ መጀመሪያ ላይ የሚገኙት 13ቱ ተማሪዎች
በመንግስት ኃይሎች ታፍነው ሲወሰዱ የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን ለማጠናቀቅ ጥቂት ጊዜያት ብቻ ይቀራቸው ነበር፡፡


በእነ እስማኤል ኑርሑሴን መዝገብ የተከሰሱትና ብይን የተሰጠባቸው ተማሪዎች እስማኤል ኑር ሁሴን፣ ሰይድ
ኢብራሂም፣ ሙሐመድ ሰይድ፣ ፈትሂያ ሙሐመድ፣ ኑርዬ ቃሲም፣ ያሲን ፈያሞ፣ መሃመድ አሚን፣ ዩሱፍ ከድር፣ ጣሂር
መሃመድ፣ መሃመድ ሰይድ፣ አብደላ መሃመድ፣ አብዲ ሙሐመድ እና ኢብራሂም ዩሱፍ ናቸው። ከተከሳሾቹ መካከል ብቸኛዋ
ሴት የህክምና ተማሪዋ ፈትህያም የክሱ ሰለባ ሆና በቃሊቲ እስር ያሳለፈች ሲሆን ከቤተሰቦቿ ጋር እንዳትገናኝም
በወህኒው ሀላፊዎች እቀባ ተጥሎባት ይገኛል፡፡


በግንቦት 2005 ክስ የተመሰረተባቸው እነዚሁ ተማሪዎች በተለያዩ ሰበብ አስባቦች ምክንያት ችሎቱ እየተጓተተ
በመቆየቱና የፍትህ ስርአቱ የዜጎችን መብት ማስከበር በማይችልበት ደረጃ በመኮላሸቱ ጥፋተኛ ሆነው ቢገኙ እንኳ
ክሳቸው ከሚያስፈርድባቸው በላይ በእስር እየቆዩ መሆኑን የህግ ባለሙያዎች ሲያሳስቡ ቆይተዋል፡፡ በዚህም ምክንያት
ፍርድ ቤቱ ዛሬ የስድስት ወር ቅጣት ሲበይን ተማሪዎቹ በእስር ከ21 ወራት በላይ (ከተወሰነባቸው ቅጣት 3 እጥፍ
በላይ) በቆዩበት ሁኔታ ላይ ነበር፡፡


እነዚህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው በእምነታቸው ምክንያት ብቻ ከሌሎች ተማሪዎች ተነጥለው በድብደባ እና
በተንዛዛ የፍርድ ቤት አሰራር መንገላታታቸው ሳያንስ የጥፋተኝነት ውሳኔ መተላለፉ አስደንጋጭም አሳዛኝም ነው፡፡
በተለይም ተማሪዎቹ ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለው ሊመረቁ የሚችሉበት ጊዜ ያለፈ እና የቀሪዎቹም የተራዘመ ሲሆን
አሁንም ቀጣይ የትምህርት እድላቸው ምን እንደሚሆን በውል አልታወቀም፡፡ በተማሪዎቹ ላይና በህዝቡ ላይ ለተዘነበለው
ፍትህ የህግ ስርአቱ ተዋንያንና አጠቃላይ አስፈጻሚው አካል ተጠያቂ ሊሆኑ እንደሚገባ እሙን ቢሆንም የፍትህ ስርአቱ
የመንግስት የፖለቲካ ማስፈጸሚያ ሸንጎ መሆኑ ሁሉንም ዜጋ ሊያሳስበው ይገባል፡፡


ህዝበ ሙስሊሙ እነዚህ ጀግና ተማሪዎች ይህን ሁሉ መስዋእትነት የከፈሉለትን ትግል ከዳር ለማድረስ ያለውን
ቁርጠኝነት እየገለጸ ከዚህ ሁሉ ስቃይ በኋላም ቢሆን ተማሪዎቹ እንዲፈቱ ውሳኔ መሰጠቱ ለቤተሰቦቻቸው እና በዱዓና
በጭንቀት ከጎናቸው ለቆመው ሁሉ መልካም ዜና መሆኑ አልቀረምና ለተማሪዎቹ እና ለቤተሰቦቻቸው ‹‹እንኳን ደስ
አላችሁ!›› እያለ ይገኛል!



ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!

ድምፃችን ይሰማ!

አላሁ አክበር!

Monday, October 13, 2014

Breaking News: ቴዲ አፍሮ ታስሮ ፍርድ ቤት ቀረበ

ዝነኛው ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ በፌደራል ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በቀረበበት ክስ ምክንያት ዛሬ ታስሮ ፍርድ ቤት ቀረበ፡፡ ድምፃዊው የቀረበበት ክስ ከስምንት ዓመት በፊት ከቀረጥ ነፃ ወደ ሃገር ውስጥ የገባችን ቢኤምደብሊው መኪና ገዝቶ ተገቢውን የቀረጥ ክፍያ ሳያጠናቅቅ ወደ ስሙ አዛውሯል የሚል መሆኑን የኢትዮጲካሊንክ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
ድምፃዊው በዚሁ ክስ መሰረት ዛሬ ረፋድ በአራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ ክሱ ከታየ በኋላ ቀርቦ የዕለቱ ዳኛ 30 ሺህ ብር በማስያዝ በዋስ እንዲፈታ ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜም የዋስ ሂደቱን ለመጨረስና ድምፃዊውን ለማስፈታት የቢሮ ሥራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ታውቋል፡፡
ለቴዲ አፍሮ መከሰስ ምክንያት የሆነችው ይህች መኪና ከዚህ ቀደም በተቀጣበት የሰው ገጭቶ ህይወት ማጥፋት ወንጀል የተከሰሰባት ነበረች፡:http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2014/08/teddy-afro.jpg

Tuesday, October 7, 2014

Ethiopian Maid pours hot water on handicapped child | Read More at ....http://goo.gl/Ov7kOW | በሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ የአካል ጉዳተኛ የሆነቸውን የአሰሪዎቿን ልጅ በፈላ ውሀ አቃጠለች የቤት ሰራተኛዋ ኢትዮጵያዊት የአካል ጉዳተኛ በሆነችው የአሰሪዎቿ ልጅ ላይ የፈላ ውሃ በማፍሰስ ጉዳት አድርሳባታለች ተብሏል፡፡ ድርጊቱ ሲፈጸም ያየው የአካል ጉዳተኛዋ የ10 ዓመት እድሜ ያለው ወንድም በአቅራቢያው ወደ ሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ በመሄድ ጉዳዩን ለፖሊስ ካስረዳ በኋላ ኢትዮጵያዊቷ ወደ እስር ቤት ህጻኗም ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡ ... See More

Maid pours hot water on handicapped child

An Ethiopian housemaid waited for her Saudi employers to go out and poured boiling water on their little handicapped daughter, a newspaper reported on Monday.

The girl’s 10-year-old brother, who was at home in the northeastern town of Hafr Al Batin, rushed to the nearby police station and reported the maid, Sabq said.

Police arrested the maid while the child was taken to hospital suffering from burns in various parts of her body.

The paper said police questioned the maid on her motives for burning that little girl, whose age was not specified.

Source:emirates247

Sunday, September 21, 2014

EthioSwedish Task Force Decorated woyane Ambassader with Rotten Fish &eggs

በስዊድን የኢትዮጵያ አምባሳደር ወ/ሮ ወይንሸትና ተላላኪዎቿ ላይ የገማ አሳ የተቀባ እንቁላል ተወረወረባቸው (ፎቶዎች እና ቪድዮ ይዘናል)




  • 134

 በስዊዲን የኢትዮጵያ አባሳደር ላይ የገማ አሳና እንቁላል እንዳይወረወርባቸው ሲከላከሉ የሚያሳይ ፎቶ

በስዊዲን የኢትዮጵያ አባሳደር ላይ የገማ አሳና እንቁላል እንዳይወረወርባቸው ሲከላከሉ የሚያሳይ ፎቶ
 በስዊዲን የኢትዮጵያ አባሳደር ላይ የገማ አሳ የተቀባ እንቁላል እንዳይወረወርባቸው ሲከላከሉ የሚያሳይ ፎቶ

በስዊዲን የኢትዮጵያ አባሳደር ላይ የገማ አሳና እንቁላል እንዳይወረወርባቸው ሲከላከሉ የሚያሳይ ፎቶ


ናቲ ማን ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው፦
“ለኢትዮጵያ ባለስልጣናት ሕዝብን ሃገር ቤት እየገደሉ ውጭ መጥቶ መዝናናት ካሁን በኋላ ፋሽኑ አልፏል” ይላሉ
በስዊድን ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን። ኢትዮጵያውያኑ ዛሬ በስዊድን የኢትዮጵያ አምባሳደርና በተላላኪዎቿ ላይ የገማ
አሳና እንቁላል ሲወረውሩባቸው ውለዋል። አምባሳደሯም ከነሃገር ባህል ልብሷ ሮጣ ስትገባ እና ተላላኪዎቿም ሲከላከሏት
የሚያሳይ ፎቶዎች እና ቪድዮዎች ተይዘዋል። በስዊዲን የኢትዮጵያ አምባሳደር ወ/ሮ ወይንሸት ታደሰ በኢትዮጵያውያኑ
በደረሰባት ከፍተኛ ተቃውሞና የገማ አሳ በተቀባ እንቁላል ውርወራ በመደናገጥ ስትሮጥ ያመሸች ሲሆን በዲያስፖራ ያለው
ኢትዮጵያዊም በገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት እና በተባባሪዎቹ ዙሪያ ትዕግስቱ ያለቀ መሆኑን ያሳየበት ዕለት ነው።


አምባሳደሯ የሚገማ አሳ የተቀባ እንቁላል ውርወራውን ፈርተው ለረዥም ጊዜ የፖሊስ ሃይል እስኪመጣ ተቀምጠው ነበር። ተጨማሪ ፖሊስ ቢመጣም ከውርወራው ሊያስጥሏት አልቻሉም።


ከዚህ በፊት በኖርዌይ፣ በቴክሳስ፣ በሚኒሶታ፣ በዋሽንግተን ዲሲ፣ በሎስ አንጀለስ ካናዳ የወያኔ ባለልጣናት
በኢትዮጵያውያን ሊያደርጉት የነበረው ስብሰባ የተስተጓጎለባቸው ከመሆኑም በላይ በሄዱበት ቦታ ሁሉ ኢትዮጵያዊያኑ
እየተጋፈጧቸው ገዳይ እና አምባገነን መሆናቸውን ሲነግሯቸው በቪድዮ ዘ-ሐበሻ ማሳየቷ ይታወሳል።


በስዊድን የኢትዮጵያ አምባሳደር ወ/ሮ ወይንሸት ላይ የተወረወረው የገማ አሳ እና እንቁላል ውርወራ በቀጣይም
የወያኔ ባለስልጣናት በሄዱበት ቦታ ሁሉ እንደሚቀጥል በየከተማው ያሉ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እያሳወቁ ነው፡፡


ዛሬ እንቁላል የተቀባ አሳ ከተወረወረባቸው የወያኔ ባለስልጣናት መካከል፡

1ኛ. ወ/ሮ ወይንሸት ታደሰ

2ማ. አቶ ዳንኤል ጠንክር

3ኛ. አቶ ሁሴን አህመድ

4ኛ. አቶ ተረፈ ቡርቃ

4ኛ. ወ/ሮ ሮማን አብዱልቃድር

5ኛ. አቶ ፈንታዬ ሮባ

6ኛ. ወ/ሮ ሮማን ሙሉጌታ ይገኙበታል።


ቪድዮውንም ይመልከቱ፦

በስዊድን የኢትዮጵያ አምባሳደር ወ/ሮ ወይንሸትና ተላላኪዎቿ ላይ የገማ አሳ የተቀባ እንቁላል ተወረወረባቸው (ፎቶዎች እና ቪድዮ ይዘናል)





  • 134

 በስዊዲን የኢትዮጵያ አባሳደር ላይ የገማ አሳና እንቁላል እንዳይወረወርባቸው ሲከላከሉ የሚያሳይ ፎቶ

በስዊዲን የኢትዮጵያ አባሳደር ላይ የገማ አሳና እንቁላል እንዳይወረወርባቸው ሲከላከሉ የሚያሳይ ፎቶ
 በስዊዲን የኢትዮጵያ አባሳደር ላይ የገማ አሳ የተቀባ እንቁላል እንዳይወረወርባቸው ሲከላከሉ የሚያሳይ ፎቶ

በስዊዲን የኢትዮጵያ አባሳደር ላይ የገማ አሳና እንቁላል እንዳይወረወርባቸው ሲከላከሉ የሚያሳይ ፎቶ

ናቲ ማን ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው፦ “ለኢትዮጵያ ባለስልጣናት ሕዝብን ሃገር ቤት እየገደሉ ውጭ መጥቶ መዝናናት ካሁን በኋላ ፋሽኑ አልፏል” ይላሉ በስዊድን ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን። ኢትዮጵያውያኑ ዛሬ በስዊድን የኢትዮጵያ አምባሳደርና በተላላኪዎቿ ላይ የገማ አሳና እንቁላል ሲወረውሩባቸው ውለዋል። አምባሳደሯም ከነሃገር ባህል ልብሷ ሮጣ ስትገባ እና ተላላኪዎቿም ሲከላከሏት የሚያሳይ ፎቶዎች እና ቪድዮዎች ተይዘዋል። በስዊዲን የኢትዮጵያ አምባሳደር ወ/ሮ ወይንሸት ታደሰ በኢትዮጵያውያኑ በደረሰባት ከፍተኛ ተቃውሞና የገማ አሳ በተቀባ እንቁላል ውርወራ በመደናገጥ ስትሮጥ ያመሸች ሲሆን በዲያስፖራ ያለው ኢትዮጵያዊም በገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት እና በተባባሪዎቹ ዙሪያ ትዕግስቱ ያለቀ መሆኑን ያሳየበት ዕለት ነው።
አምባሳደሯ የሚገማ አሳ የተቀባ እንቁላል ውርወራውን ፈርተው ለረዥም ጊዜ የፖሊስ ሃይል እስኪመጣ ተቀምጠው ነበር። ተጨማሪ ፖሊስ ቢመጣም ከውርወራው ሊያስጥሏት አልቻሉም።
ከዚህ በፊት በኖርዌይ፣ በቴክሳስ፣ በሚኒሶታ፣ በዋሽንግተን ዲሲ፣ በሎስ አንጀለስ ካናዳ የወያኔ ባለልጣናት በኢትዮጵያውያን ሊያደርጉት የነበረው ስብሰባ የተስተጓጎለባቸው ከመሆኑም በላይ በሄዱበት ቦታ ሁሉ ኢትዮጵያዊያኑ እየተጋፈጧቸው ገዳይ እና አምባገነን መሆናቸውን ሲነግሯቸው በቪድዮ ዘ-ሐበሻ ማሳየቷ ይታወሳል።
በስዊድን የኢትዮጵያ አምባሳደር ወ/ሮ ወይንሸት ላይ የተወረወረው የገማ አሳ እና እንቁላል ውርወራ በቀጣይም የወያኔ ባለስልጣናት በሄዱበት ቦታ ሁሉ እንደሚቀጥል በየከተማው ያሉ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እያሳወቁ ነው፡፡
ዛሬ እንቁላል የተቀባ አሳ ከተወረወረባቸው የወያኔ ባለስልጣናት መካከል፡
1ኛ. ወ/ሮ ወይንሸት ታደሰ
2ማ. አቶ ዳንኤል ጠንክር
3ኛ. አቶ ሁሴን አህመድ
4ኛ. አቶ ተረፈ ቡርቃ
4ኛ. ወ/ሮ ሮማን አብዱልቃድር
5ኛ. አቶ ፈንታዬ ሮባ
6ኛ. ወ/ሮ ሮማን ሙሉጌታ ይገኙበታል።
ቪድዮውንም ይመልከቱ፦


Friday, September 19, 2014

አነጋፋው አርቲስት ሀይማኖት ዓለሙ ከሰሞኑ ባጋጠመው ህመም ዛሬ ከሰዓት ከዚህ ዓለም ተለይቷል፡፡

አሳዛኝ ዜና !!
አርቲስት ሃይማኖት ዓለሙ ከዚህ ዓለም ተለየ፡፡
አነጋፋው አርቲስት ሀይማኖት ዓለሙ ከሰሞኑ ባጋጠመው ህመም ዛሬ ከሰዓት ከዚህ ዓለም ተለይቷል፡፡
ወዳጄ ዘካሪያስ ብርሃኑ ባካፈለኝ መረጃ መሰረት
አርቲስት ሀይማኖት…በትወና /አክቲንግ/ በአሜሪካን አገር በሁለተኛ ዲግሪ
ተምሯል፡፡
በአዲስ አበባ ዪኒቨርሲቲና ራክማኖቭ ኮሌጅ ትወናን
አስተምሯል፡፡
የሲሳይ ንጉሱን ልቦለድ /ግርዶሽ/ ወደ ፊልም በመቀየርአዘጋጅቷል፤ ተውኗል፡፡
የሸክስፒርን ስራዎች በተለይም በጫንያለው
ወልደጊዮርጊስና ቴዎድሮስ ተሰማ የተተረጎመውን
ተጫወቷል፡፡
በተለይም በፀጋዬ ገብረ መድህን ስራዎች በዘመኑ እጅግድንቅ ብቃት ያሳየባቸውን የእናት ዓለም ቀኑ እና ሀሁበስድስት ወር ቴአትሮች ገፀባህሪያት በብሔራዊ ቴአትርተውኗል፡፡
ሀምሌትን አዘጋጀቷል፡፡
ከፍቃዱ ተክለማሪያም በፊት ቴዎድሮስን ሆኖ ተወኗል፡፡
ጊታር በድንቅ ብቃት ይጫወት ነበር፡፡
በሲዲ ያልተለቀቁ የእንግሊዝኛ ዘፈኖች አሉት፡፡ ከምንም በላይ ግጥም በማራኪ አቀራረብ በማንበብ
ይወደድ የነበረው አነጋፋው አርቲስት ሀይማኖት ዓለሙበመድረክ መምራትም ተወዳጅ ነበር፡፡
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በማስታወቂያው ዘርፍ ተሰማርቶእየሰራ የነበረው ሀይማኖት ባደረበት ህመም ከዚህ ዓለምተለይቷል፡፡

ኤርትራዊው ባል ኢትዮጵያዊት ሚስቱን ገደለ፡፡

Admas News Husband Killed his Wife ...

Stockholm:- Marta Bogale has been living in Stockholm, Sweden for 23 years, her husband, whose name is not mentioned, came to Sweden 6 years ago from Asmara, Eritrea. They knew each other when they used to work on the same company in Stockholm.

After they started dating, they eventually got married and moved together. She is 32 and he is 29. As sources told Admas Radio, after they started to live together, they tried to have a wedding ceremony 2 years ago but the ceremony was postponed on his request for unknown reasons.

Recently, in August 2014, She gave a birth to a baby boy. But 3 weeks after she gave a birth, Police said the husband stabbed her repeatedly to death. The news was a shock to the Ethiopian Community in Stockholm. Her father, who saw her body, fainted but recovered in the hospital the next day. The husband sent to jail and her body was buried in "Heliga Korsets kapell Skogskyrkogarden" cemetery in Stockholm.

Reason for killing is not known yet. (Source Admas Radio ATLANTA)
[Pic. The couples during the good times]

Source: Admas News Atlanta

Thursday, September 18, 2014

My fiance who came from Ethiopia to U.S is pregnant from her ex-boyfriend

http://www.amharictube.com/article_read.php?a=536
Read in English: http://soderetimes.com/?p=6017
እጮኛዬ ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ ስትመጣ ከቀድሞ ጓደኛዋ አርግዛ መጣች
ምንጭ አድማስ ዜና - ትርጉም በሶደሬ
ከ 17 ወር በፊት ኢትዮጵያ ለአንድ ወር እረፍት ሄጄ ነበር። እና ከአንድ ልጅ ጋር እተዋወቃለሁ። በጣም ሰለወደድኳት እርፍቴን በሁለት ወር አራዝምኩኝ። ከመምጣቴ በፊት የእንጋባ ጥያቄ አቀርብኩላት። እሷም ተስማማች።... See More

Tuesday, September 16, 2014

13-year-old boy | Read More at .... http://goo.gl/S8BAc4 | የ31 ዓመቷ የቤት ሰራተኛ ከ13 ዓመት ታዳጊ አረገዘች በባህሬን የቤት ሰራተኛ የሆነችው የ32 ዓመቷ ፊሊፒናዊት የቤት ሰራተኛ የ13 ዓመት እድሜ ካለው የአሰሪዎቿ ልጅ አርግዛለች፡፡ የቤት ሰራተኛዋ በመጀመሪያ በልጁ እንደተደፈረች ብትናገርም በኋላ ላይ ግን በፍላጎቷ ድርጊቱን መፈጸሟን ተናግራለች፡፡ የ13 ዓመቱ ታዳጊ በቤሩት ‹‹ወጣቱ የልጅ አባት›› ይሆናልም ተብሏል፡፡ የ31 ዓመቷ የቤት ሰራተኛ ከ13 ዓመቱ የአሰሪዎቿ ልጅ ጋር በድብቅ ግንኙነት ፈጥራ እንደነበር አምናለች የተባለ ሲሆን እርግዝናዋንም ለመደበቅ ብዙ ትራ እንደነበረ ተነግሯል፡፡

Maid impregnated by 13-year-old boy

A 32-year-old Indonesian housemaid in Manama gave birth to a baby boy after she was impregnated by her employer’s 13-year-old son, the youngest father in Bahrain.

The maid, who is on trial in the Gulf island nation, had first claimed the boy raped her, but changed her statements after she was pressed by police investigators.

The boy’s lawyer Ibtisam Al Sabbagh, quoted by CNN Arabia satellite TV news channel, said the maid had managed to hide her pregnancy from her employers for several months before she was about to board a flight for her home country.

“But she went into premature labour before her travel. She delivered herself in the bathroom at her employer’s home,” she said.

“She had first claimed she was raped by the boy, who is considered a child, but it emerged later that she had a relationship with him.”

emirates247

Sunday, September 14, 2014

ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ 17 የውጭ ዜጎች ክስ ተመሠረተባቸው

• ከ95 ሚሊዮን ብር በላይ የገቢ ንግድ ግብርና ቫት ባለመክፈላቸው ተከሰዋል • ከ716 ሚሊዮን ብር በላይ ምንጩንና ዝውውሩን ደብቀዋል ተብሏል • ከ104 ሚሊዮን ብር በላይ በሕገወጥ መንገድ መገኘቱ ተገልጿል
newsየፀና የንግድ ፈቃድ ሳይኖራቸው የንግድ ሥራ በመሥራት፣ የንግድ ትርፍ ግብር፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ ባለመክፈል፣ በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ በማቅረብና ሐሰተኛ ሰነዶችን በማቅረብ ወንጀል የተጠረጠሩ የሲሪላንካ፣ የህንድ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ፣ የጂቡቲ፣ የኒውዚላንድና ኢትዮጵያውያን 17 ግለሰቦች ክስ ተመሠረተባቸው፡፡
የገቢ ግብርና ቫት ባለመክፈል፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ምንጭና ዝውውር በመደበቅና በሕገወጥ መንገድ በመያዝ ተከሰዋል፡፡
የፌዴራል ግለሰቦች ዓቃቤ ሕግ ጳጉሜን 4 ቀን 2006 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት ክስ የመሠረተባቸው፣ ተጠርጣሪዎች ኢትዮጵያውያን አሽረፍ አወል አብዶና በሥራ አስኪያጅነት የሚመሩት አካፔ ኢምፔክስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ የሲሪላንካ ዜጋ የሆኑት ሂትራጅግ ያሳንታ ሱሬንድራናታ፣ ፕላንዋታጅ አሲታ፣ ቦፒ ጊድራ አጅት፣ አሳንታ ኡዳያ፣ ኩሩፑ አራችችግ፣ የህንድ ዜግነት ያላቸው አንኪት ሙኪሽ መሂታ፣ አሾክ ሞሃንላል፣ ኩማር ኤም፣ ቪሻል ኩማርና ሙኒሽ ኩማር፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ ዜግነት ያላቸው መሐመድ ሽፋን መሐመድ፣ ኦቶ ወርልድ ኢንተርናሽናል ፍሪዞን ኩባንያና ዱባይ ኦቶ ጋላሪ ኤልኤልሲ፣ የኒውዚላንድ ዜጋ ሱሀስ ፓራሳድና የጅቡቲ ዜግነት ያላት ሲና መሐመድ መሐሙድ ይባላሉ፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በተለይ ዱባይ ኦቶ ጋለሪ ኤል.ኤል.ሲና ኦቶ ወርልድ ኢንተርናሽናል ፍሪዞን ኩባንያዎች፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የሚገኘውን አካፔ ኢምፔክስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር እንደ ሽፋን በመጠቀም የወንጀል ድርጊት መፈጸማቸውን ክሱ ያብራራል፡፡
የሲሪላንካ ዜግነት ያላቸው ሂትራጅግ ያሳንታ ሱሬንድራናታ ሂትያራጅጅ (ሱሬንድራ)ና ፕላን ዋታጅ አሲታ ሳራናታ ፔሬር (አሲታ) ድርጅቶችን በሚመለከት ሁለት የሲሪላንካ ዜጐች በኢትዮጵያ የዱባይ ጋለሪ መሪና ረዳት መሪ በሚል ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውንም ክሱ ያስረዳል፡፡ ዱባይ ኦቶ ጋለሪና ኦቶ ወርልድ ኢንተርናሽናል ኩባንያዎች፣ በኢትዮጵያዊው አሽረፍ አወልና የጅቡቲ ዜግነት ባላት ሲና መሐመድ ባለቤትነት የተቋቋመውን አካፔ ኢምፔክስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበርን በሽፋንነት በመጠቀም፣ ሐሰተኛ የሥራ ውል መፈራረማቸውም በክሱ ተጠቅሷል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ምንም ዓይነት የፀና የሥራ ፈቃድ ሳይኖራቸው፣ ለኢትዮጵያውያን ብቻ የተከለለና ለውጭ ዜጎች ባልተፈቀደ የንግድ ሥራ ዘርፍ በመሰማራት፣ የባጃጅ ምርትና መለዋወጫ በቀጥታ ከዱባይ ወደ አገር ውስጥ ሲያስገቡ እንደነበር ክሱ ያስረዳል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ጂቡቲ ውስጥ ከሚገኝ የንግድ ድርጅት ኤስዲሲ በርበራ ፍሪዞን ኩባንያን በመጠቀም በጂቡቲ በኩል ወደ ኢትዮጵያ በማስገባት፣ በኢትዮጵያ በሚገኙ ክልሎች፣ ዞኖችና የወረዳ ከተሞች በመዘዋወር የገበያ ጥናትና ሌሎች ተያያዥ የንግድ ሥራዎችን በመሥራት ለዱባይ ኦቶ ጋለሪ ኤልኤልሲ ሪፖርት ሲያደርጉ መገኘታቸውን ክሱ ያብራራል፡፡
ሌሎቹ ተጠርጣሪዎች ኢትዮጵያ ውስጥ በተቋቋመው አካፔ ኢምፔክስ ተቀጣሪ ሠራተኞች በመምሰል፣ ሐሰተኛ የሥራ ቅጥር ውል በመፈራረምና በድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ኢትዮጵያዊው አቶ አሽረፍ አወልና በድርጅቱ ተጠያቂነት በሌላ የሥራ መደብ ፈቃድ በማውጣት ሲጠቀሙ እንደነበርም ክሱ ይገልጻል፡፡
ህንዳዊው አሾክ ሞሃንላል ሻርማና ኒውዚላንዳዊው ሱሀስ ፓራሳድ በቱሪስት ቪዛ ወደ አገር ውስጥ ገብተው፣ ያለምንም የሥራ ፈቃድ የባጃጅ መለዋወጫ ሽያጭ ንግድ ሥራ ውስጥ በመሰማራት በክልሎች በሚገኙ የዞንና የወረዳ ከተሞች በመዘዋወርና የገበያ ጥናት በማድረግ፣ ለዋና ድርጅታቸው ሪፖርት ሲልኩ መገኘታቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ያቋቋሙትን አካፔ ኢምፔክስ በሽፋንነት በመጠቀም ለኢትዮጵያውያን ባለሀብቶች ብቻ የተከለለና ለውጭ ዜጎች በማይፈቀድ የአስመጭነት፣ የጅምላና የችርቻሮ ንግድ ሥራ ውስጥ ተሰማርተው መገኘታቸውንና ምንም ዓይነት የሥራ ፈቃድና የፀና የንግድ ፈቃድ ሳይኖራቸው ሽፋን በመስጠት፣ በቱሪስት ቪዛ ብቻ የባጃጅ ንግድ ሥራ እንዲሰማሩ መደረጋቸውን ክሱ ያብራራል፡፡
አካፔ ኢምፔክ፣ ዱባይ ኦቶ ጋለሪ ኤልኤልሲና ኦቶ ወርልድ ኢንተርናሽናል ፍሪዞን ኩባንያዎች ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥሮችን የወሰዱ ቢሆንም፣ የፀና የንግድ ፈቃድ ሳይኖራቸው ለውጭ ባለሀብት የማይፈቀድ ሥራ ላይ በመሰማራት ካገኙት ገቢ ግብር አለመክፈላቸውን ክሱ ያብራራል፡፡ በመሆኑም ሐሰተኛ ሰነድ በማቅረብ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ የገቢ ንግድ ግብርና ተጨማሪ እሴት ታክስ አለመክፈላቸውን ክሱ ይጠቁማል፡፡ ከ416 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆን ገንዘብ ምንጩንና ዝውውሩን መደበቃቸው ተጠቅሷል፡፡ እንዲሁም ከ104 ሚሊዮን ብር በላይ በኢትዮጵያዊው አሽረፍ አወልና በድርጅቱ አካፔ ኢምፔክስ ስም በተለያዩ ባንኮች በማስቀመጥ፣ በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስለው ማቅረባቸውን ክሱ ይዘረዝራል፡፡
ህንዳዊው ቪሻል ኩማር ላክሃኒ ደግሞ የባጃጅ መገጣጠሚያና ማምረቻ ንግድ የሥራ ዘርፍ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ የኢንቨስትመንት ፈቃድና የንግድ ፈቃድ በማውጣት፣ እንዲሁም ኤሽያ አፍሮ አውቶሞቢልስ በሚል ከንግድ ሚኒስቴር በተሰጠው የንግድ ስያሜ ቪሻል ኩማር ላክሀኒ የሚል ድርጅት ማቋቋሙን ክሱ ይጠቁማል፡፡ ነገር ግን የመገጣጠሚያ ፋብሪካውን ሳያቋቁምና ምንም ዓይነት የአስመጪነት፣ የአከፋፋይነትና የችርቻሮ የፀና የንግድ ፈቃድ ሳይኖረው፣ ባጃጅ ከውጭ አገር በማስመጣት ሳይገጣጠም በጅምላና በችርቻሮ ሲሸጥ እንደነበር በክሱ ተካቷል፡፡ ተጠርጣሪው ከ84 ሚሊዮን ብር በላይ የገቢ ግብርና ተጨማሪ እሴት ታክስ ካለመክፈሉም በላይ፣ በሕገወጥ ንግድና ግብር ሲሠራ ያገኘውን ከ330 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ገንዘብ፣ ከወንጀል ተጠያቂነት ለማምለጥ በማሰብ የገንዘቡን ምንጭና ዝውውር መደበቁን ክሱ ያብራራል፡፡
የጂቡቲ ዜግነት ያላት ተጠርጣሪ ሲና መሐመድ መሐሙድ በተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ በዱባይ የኢትዮጵያ ቆንሲላ ጽሐፈት ቤት ቀርባ፣ ‹‹የቤት እመቤት›› የሚል ሐሰተኛ መረጃ በመስጠት መታወቂያ በማግኘት ስትገለገልበት በመክረሟና ሐሰተኛ የሆነ ኦፊሴላዊ ሰነድ በማጭበርበር ማግኘት ወንጀል መከሰሷን የዓቃቤ ሕግ ክስ በዝርዝር ያሳያል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በአጠቃላይ ከ95 ሚሊዮን ብር በላይ የገቢ ንግድ ግብርና ቫት ባለመክፈል፣ ከ716 ሚሊዮን ብር በላይ ምንጩንና ዝውውሩን በመደበቅ፣ እንዲሁም ከ104 ሚሊዮን ብር በላይ በሕገወጥ መንገድ በመያዝ ክስ ተመሥርቶባቸዋል፡፡
የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች ለደንበኞቻቸው የዋስትና መብት እንዲጠበቅላቸው በጽሑፍ ለፍርድ ቤቱ በማቅረባቸው፣ ዓቃቤ ሕግ ለጥያቄው በጽሑፍ ምላሽ እንዲሰጥ ለመስከረም 6 ቀን 2007 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡

Monday, September 8, 2014

ኢህአዴግ በአንድ አመት ውስጥ ለተለያዩ ዝግጅቶች ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ ማውጣቱ ተሰማ

Today, September 08, 2014, 
ጳጉሜን ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአለፈው አንድ አመት ውስጥ ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ለፓርቲው የፖለቲካ ስራ የሚጠቅም ከመንግስት ባጀት ከ900 ሚሊዮን ብር ያላነሰ ገንዘብ ማውጣቱን ምንጮች ገለጹ።

ለብሄር ብሄረሰቦች ቀን፣ ለባንዲራ ቀን፣ ለመከላከያ ቀን፣ ለተለያዩ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የፖለቲካ ስልጠና፣ ከ100 ሺ በላይ ለሚሆኑ የኢህአዴግ አባላት ስልጠና፣ ለፖሊስ ሰራዊት የተሰጠው ስልጠና፣ እንዲሁም በተለያዩ ታሃድሶ የሚል ስያሜ በተሰጣቸው ስልጠናዎችና ስብሰባዎች ከመንግስት ባጀት እስከ 900 ብር ወጪ መደረጉን እስካሁን የተሰባሰቡት የወጪ ደረሰኞች እንደሚያሳዩ ምንጮች ገልጸዋል።

አንዳንድ ወጪዎችን ክልሎች ቢያወጡዋቸውም ፣ ወጪው ከመንግስት ባጀት የሚሸፈን መሆኑን የጠቀሱት ምንጮች፣ አሃዙ ተጠቃሎ ሲታወቅ ወጪው ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል።

ገዚው ፓርቲ ለራሱ የፖለቲካ ስራ በተለያዩ ሰበቦች ገንዘብ ከመንግስት ካዝና ማውጣት መቀጠሉ፣ ታክስ ከፋዩ ህዝብ በተዘዋዋሪ መንገድ ሳይፈልግ ፓርቲውን እዲደግፍ እያደረገው መሆኑንና የአገሪቱ አጠቃላይ ኦዲተሮችም ይህን ወጪ እንደመንግስት ወጪ በመያዝ ፓርቲውን ተጠያቂ ለማድረግ እንዳልቻሉ ምንጮች አክለው ተናግረዋል።

በተለይ የብሄር ብሄረሰቦች ፣ የባንዲራ እና የመከላከያ ቀን በሚባሉት ዝግጅቶች የአንድ አካባቢ ሰዎች ተሰባስበው እነሱ በመሰረቱት የዝግጅት ኩባንያ ዝግጅት በማዘጋጀት ከፍተኛ ገቢ እንደሚያገኙ የጠቆሙት ምንጮች፣ እነዚህ ሰዎች ከመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በፈጠሩት ሽርክና የተለያዩ ሃሳቦችን
እያመጡና እና እያስጸደቁ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ በመመዝበር ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ግንባሩ ከዚህ ቀደም ለኤች አይ ቪ ቫይረስና ለሌሎችም በሽታዎች መከላከያ የሚመጡ ፈንዶችን ሲጠቀም መቆየቱን ያስታወሱት ምንጮች፣ በተለይ ግሎባል ፈንድ የተባለው አለማቀፍ ለጋሽ ድርጅት ለኢትዮጵያ ይሰጥ የነበረውን እርዳታ መቀነሱን ተከትሎ፣ ኢህአዴግ ሙሉ በሙሉ የመንግስትን ባጀት በመጠቀም
የፖለቲካ ስራ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። አንዳንድ ዝግጅቶች በመንግስት ስም እውቅና ቢሰጣቸውም ዋና ተልእኮዋቸው የኢህአዴግን አብዮታ ዲሞክራሲ

ፖሊሲ ማንጸባረቅ መሆኑን ምንጮች አያይዘው ተናግረዋል።

Sunday, September 7, 2014

የለውጡ አካል መሆኛው ግዜው አሁን ነው

September 7/2014

እኔም አንዳርጋቸው ነኝ የሚል ድምፅ ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ እያሰተጋባ ነው። ይሄን ድምፅ የሚያቆመው አንዳችም ምድራዊ ኃይል አልተገኘም። ኢትዮጵያዊ ባለበት ሥፍራ ሁሉ ይሄ ድምፅ ከፍ ብሎ እየተሰማ ነው። ይህንንም ተከትሎ “ላንቺ ነው ኢትዮጵያ፤ ላንቺ ነው ኢትዮጵያ” የሚለው መዝሙር በኢትዮጵያ ተራሮች እናት ላይ እየተዘመረ ነው። ፍትህ ተዋርዳለች፤እኩልነት ጠፍቷል፤ ነፃነት የለም ያሉ ምርጥ ኢትዮጵያዊያን ሳያቅማሙ አያቶቻቸው በተመላለሱበት ተራሮች ላይ ተሠማርተዋል። ሞትንም ንቀው ጋሻ አንስተዋል፤ ሰይፋቸውንም መዘዋል። ለፍትህ፤ ለዕኩልነት እና ለነፃነት የተመዘዘው ሰይፍ ከእንግዲህ ወደ ሰገባው እንደማይመለስ ህወሃቶች እንዲያውቁት እንፈልጋለን።
በኢትዮጵያችን ፍትህ ከጠፋ ብዙ ዘመን ሁኖታል። ከሁሉም ዘመን የህወሃቶች ዘመን ግን የተለየ ነው። ህወሃቶች ህግን ዜጎችን የማጥቂያ መሣሪያ አድርገው መጠቀማቸው ከሌሎች እንዲለዩ ያደርጋቸዋል። እነዚህ ቡድኖች ሥፍር ቁጥር የሌላቸው ቂም መወጣጪያ ህጎችን አውጥተዋል። እንዲህ በማድርጋቸውም ሠላም እናገኛለን ብለው ያስባሉ። የህወሃቶች አስተሳሰብ ደካማና እርባና ቢስ መሆኑን ከሚያሳዩ ተግባሮቻቸው መካከል አንዱ ይሄው በፍትህ ሳይሆን በህግ ብዛት ሠላም እናገኛለን ብለው ተስፋ ማድረጋቸው ነው። የህግ ብዛት ሠላምን አያስገኝም፤ ፍትህንም ማስፈን አይችልም። እንዲያውም ህግ በበዛ ቁጥር ፍትህ እየጎደለች እንደምትሄድ የህወሃቶች ድርጊት ደህና ምስክር ነው። እነርሱ ዜጎችን ለመበቀያ ብለው የሚያወጧቸው ጥቃቅን ህጎች እነርሱ “ህገ መንግስት” ብለው የሚጠሩትን የሚንዱ እና ፍትህን ዋጋ የሚያሳጡ ሁነው እያየናቸው ነው። የፀረ ሽብር ህጉ በህገ መንግስቱ የተቀመጠውን የዜጎችን የመናገር የመደራጀትና በሰላማዊ መንገድ የመንግስትን እኩይ ተግባራት የመቃወምን መብት የገፈፈ ነው። የፀረ ሙስና ህጉም ቢሆን እንዲሁ ነው። በፀረ ሙስና ህጉ የሚጠየቁ በህወሃት የተጠሉ ብቻ ስለመሆናቸው በሙስና የተጨማለቁት የህወሃት ሹማምንት ህያው ምስክሮች ናቸው። በህወሃቶች ህግ ሁሉም ዜጎች እኩል አይደሉም። ህወሃቶች ከሌሎች ይበልጣሉ። የህወሃቶች ምኞት እነርሱ ከህግ በላይ፤ ሌላው ህዝብ ከህግ በታች ሁነው ህወሃትን ተሸክመው እንዲኖሩ ነው። እንዲህ ዓይነቱን ኢ-ፍትሃዊነት መታገል ግዜው የሚጠይቀው ታሪካዊ ግዴታ ነው። መሪያችን አንዳርጋቸው ፅጌ የተነሳውም ህወሃቶች መሣቂያ መሳለቂያ ያደረጓትን ፍትህ ወደ ሚገባት ክብር ለመመለስ ነው። በአገራችን የህግ የበላይነት ሠፍኖ ጥቂቱ ብዙሃኑን ሳይጫን፤ ማንም ማንንም ሳይሸከም ሁሉም በህግ እና በፍትህ እኩል ሁኖ የሚኖሩባት ሠላም የበዛላት ሥፍራ እንድትሆን የመሪያችን የአንዳርጋቸው ምኞት ነው። ይሄን ምኞት ሚሊየኖች አንግበው ተነስተዋል።
ህወሃቶች አገራችንን አደጋ ላይ ከጣሉባቸው አንኳር ድርጊቶቻቸው መካከል አንዱ በዜጎች መካከል እየፈጠሩ ያሉት ግልፅ ልዩነት ነው። ህወሃቶች ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር እኩል ነን የሚል እምነት የላቸውም። የህወሃቶች ዕምነት እነርሱ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ከፍ እንደሚሉና በዚያች አገር ውስጥ የተለየ መብት እንዳላቸው ነው። ለመገድልም፤ ለመዝረፍም፤ዜጎችን ለማሳቃየት እና ከአገር ለማባረርም መብቱ የእኛ ነው የሚል ጅላጅል እምነት አላቸው። ይህ የሞኝ እምነታቸው በዜጎች መካከል ቂመ በቀል ሊያተርፍ የሚችል አድሎዎ እንዲፈጥሩ አድርጓቸዋል። አድሎአቸውንም ይበልጥ የከፋ የሚያደርገው ህወሃቶች ሁሉን አድራጊ እኛ ነን ብለው ሲያበቁ የህወሃት የበላይነት የለም ብላችሁ እምኑ ብለው ዜጎችን መጫናቸው ነው። ይህ ድርጊታቸው ብዙ ዜጎችን አስቆጥቷል። ህወሃቶች ግን የዜጎችን ቁጣ የሚያይ ዓይን፤ የሚያስተውል ሂሊና ርቋቸዋል። በኢትዮጵያችን በህወሃቶች አማካኝነት እየተፈጠረ ያለው ግልፅ አድልዖ ለአገራችን ህልውና ከፍተኛ አደጋ ነው። በህዝብ መካከል አድልዖ መፈፀም እና ቂምና በቀልን መትከል የህወሃቶች የመኖሪያ ድንኳናቸው ሁኗል። መከፋፈልና አድልዖ ባለበት አገር ውስጥ ሠላም ይኖራል ማለት አይቻልም። አድልዎ የታላላቅ ግጭቶችና ለውጦች ጥሩ ምክንያት መሆኑን መርሳት አይገባንም።መሪያችን አንዳርጋቸውም ሆነ ግንቦት ሰባት ንቅናቄ የተነሳው እንዲህ በዜጎች መካከል የሚፈፀመውን አድልዖ ለማስቆምና ዜጎች በገዛ አገራቸው በእኩልነት የሚኖሩበትን ሁኔታ ለመፍጠር ነው። ይህ የእኩልነት ጥያቄ የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ዜጎች ጥያቄ ሁኖ ከኢትዮጵያ እስከ ውጪ አገራት ድረስ እያሰተጋባ ነው።
ሌላው ህወሃቶች አገሪቷን እያዋረዱ ካሉበት ነገሮች መካከል አንዱ የነፃነት ጥያቄ ነው። እኛ ከመጣን በኋላ በኢትዮጵያ ነፃነት ሰፈነ እያሉ ያላዝናሉ። ህወሃቶች ከነፃነት ጋር ተያይዞ ሊመጣ የሚችለውን ኃላፊነት ለመረዳትና ለመሸከም ከፍተኛ የሆነ የአስተሳሰብ ድክመት አለባቸው። ከነፃነት ጋር የሚመጣውን ኃላፊነት ለመሸከም ብቻ ሳይሆን የነፃነትንም ትርጉም ለመረዳት ከፍተኛ የሆነ የእውቀት ማነስ ችግር ያለባቸው መሆኑም ይታወቃል። ራሳቸውን ከታሰሩበት የድንቁርና ሰንሰለት ማስፈታት ሳይችሉ ከሰሞኑ የከፍተኛ ተቋም ተማሪዎችን ሰብስብው የእኛን አብዮታዊ ዲሞክራሲ ካልስተማርናችሁ ትምህርታችሁን አትቀጥሉም ሲሉ ማሰብ ማቆማቸውን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳየን አንድ እውነት ሁኖ አግኝተነዋል። ማሰብ የሚችሉ ቢሆኑማ ኑሮ ነፃነት ማለት ‘የእናንተን አብዮታዊ ዲሞክራሲ መስማት አልፈልግም ማለትን’ እንደሚጨምር ያውቁ ነበር። ነፃነትን የማያውቁት ነፃ አውጪዎች ነን ባዮቹ ህወሃቶች ግን ተማሪው መስማት የማይፈልገውን አብዮታዊ ዲሞክራሲ አስገድደው እየጋቱት ይገኛሉ። ለሚቀጥለውም አርባና ሃምሳ ዓመት ስልጣኑን ለማንም አሳልፈን የምንሰጥ አይደለንም ሲሉ በድፍረት ተናግረዋል። የዚህ ሁሉ ድፍረት ምንጭ ህወሃቶችን የተፀናወታቸው እኔ ብቻ ከሚል ከንቱ አስተሳሰብ የመነጨው ስግብግብነታቸው መሆኑን መገነዘብ ያስፈልጋል።
እንግዲህ ፍትህ መቀለጃ ሁናለች፤ እኩልነት ተጓድሏል፤ ነፃነት ጠፍቷል የሚሉ ዜጎች ከሁሉም አቅጣጫዎች ድምፃቸውን እያሰሙ ነው። የህዝቡ ብሶትም ፅዋውን ሞልቶ እየፈሰሰ ነው፤ ቁጭቱም ከመቸውም ግዜ በላይ ግሏል። ከሰሞኑ በሃያ ስድስት ታላላቅ ከተሞች የተደረጉት ውይይቶችም ያሳዩን አንድ እውነት ህዝቡ ይበልጥ መቆጣቱን ነው። ቁጣውም የተገለፀበት መንገድም ሌላው አስደማሚ ጉዳይ ነው።“እኛም አንዳርጋቸው ነን” ሲሉ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው አሰምተዋል። ከእንግዲህ ፍርሃት ሆይ መወጊያህ ወዴት አለ የሚሉ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ላንቺ ነው ኢትዮጵያ፤ ላንቺ ነው ኢትዮጵያ እያሉ ዘምረዋል። ይሄ ለፍትህ፤ ለእኩልነትና ለነፃነት ለሚታገሉ ታጋዮች ተስፋ ሰጪ ምልክት ነው።
ህወሃቶች በሠላማዊ መንገድ ለሚደረገው ትግል መንገዱን ሲያደናቅፉ እሰከ ዛሬ ዘልቀዋል። አሁን ጭራሹን ገና ሃምሳ የመከራ ዘመን እየተመኙልን ነው። ይሄ ምኞታቸው ቅዥት ሁኖ እንደሚቀር እኛ ልናስታውሳቸው እንፈልጋለን። በዚያች አገር ለውጥ መምጣት አለበት። ለውጡ በዛፍ ላይ የተንጠለጠለ የጎመራ ፓፓያ አይደለም በራሱ ወደ ምድር የሚወርድ፤እኛ ራሳችን ልናወርደው የሚገባን እንጂ። ተፈላጊውን ለውጥ ለማምጣት እያንዳንዱ ዜጋ በቻለው መሣሪያና ባለው አቅም ሁሉ ለልውጡ ሳያቅማማ መታገል ይኖርበታል። ህወሃቶች ነፃነታችንን አይሰጡንም፤ ፍትህም ከእነርሱ እጅ የምትገኝ አይደለችም፤ እኩልነትንም የሚያውቁ አይደሉም እነዚህ ወርቃማ እሴቶች በትግል የሚገኙ ናቸው። እነዚህን ክቡር ስጦታዎች አስነጥቆ ዝም ያለ ወደ መታረጃው ሥፍራ የሚነዳ ከብትን ይመስላል። ብዙ ኢትዮጵያዊያን እንዲህ መሆንን የሚምርጡ አይደሉም። በየከተሞቹ በተደረገው ውይይት ከተገነዘብናቸው እውነቶች መካከል አንዱ ዜጎች ለፍትህ፤ለእኩልነት እና ለነፃነት አስፈላጊውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ነው።
በህወሃት ዘመነ መንግስት የመከራ እንባችሁን በመዳፋችሁ የምታፍሱ፤ ህወሃት በአገሪቷ ላይ እያደረሰ ያለው የጥፋት ድርጊት የሚያነገበግባችሁ እና ምን እናድርግ መሪ አጣን የምትሉ ስሙን! መሪ ካጣችሁ እንዲህ አድርጉ “ራሳችሁ ተነሱና መሪ ሁኑ!”። ከምታምኗቸው ጥቂት ወዳጆቻችሁ ጋር ሁናችሁ ተደራጁ፤ አንዳችሁ አንዳችሁን አድምጡ፤ ጥሩ ተመሪ መሆን ከቻላችሁ ጥሩ መሪ ወጥቷችኋል ማለት ነው። የአገራችን ፈርጀ ብዙ ችግር በጥቂት ዜጎች ብቻ የሚቀረፍ አይደለም።የሁሉንም ቁርጠኛ ዜጎች ትግል የሚጠይቅ ነውና በየመንደራችሁ ተደራጅታችሁ የጎበዝ አለቃ መርጣችሁ ዘረኞችን፤ ዘራፊዎችንና አድሎዋዊ ሥርዓት የዘረጉባችሁን ታገሏቸው። እንዲህ ካደረጋችሁ ከእኛ ጋር ለመገናኘት መንገዱ ቀላል ይሆናል።
የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጥያቄ አጭርና ግልፅ ነው። ፍትህ፤ ነፃነትና እኩልነት በኢትዮጵያችን ይሰፈን ነው። የህወሃትን ዘረኝነትና አምባገነንነት የሚፀየፍ ሁሉ የንቅናቄያችን ደጋፊ ነው። እነዚህን ነገሮች በኢትዮጵያ ለማስፈን በሚችለው ሁሉ ርምጃ መውሰድ የጀመረ የንቅናቄያችን አካል ነው። እኛም ከጎኑ አለን። እንዲህ በማድረግ የማይቀረውን ለውጥ አናመጣለን። ለውጡ ይመጣል አንድም የተፈጥሮ ህግ ስለሆነ፤ አንድም ደግሞ እኛ ሳናቅማማ የፈለግነውን ለውጥ ለማምጣት ስለተነሳን።
ህወሃቶች መስልጠን የማይችሉ፤ ከአዲስ አስተሳሰብ ጋር ራሳቸውን ማዋሃድ የማይሆንላቸው ፍፁም ግትሮች መሆናቸውን በተዳዳጋሚ አይተናል። ይሄን ግትርነታቸውን እንደ ጀግንነት ይቆጥሩታል። በአገራችን ደህና አባባል አለች እንዲህ የምትል “ሞኝ አሸነፈ ምን ብሎ? እምቢ ብሎ” ይባላል። ህወሃቶችን በዚህ አባባል መግለፅ ሞኝ ያስመስላቸዋል እነርሱ ግን ሞኞች አይደሉም ጨካኞች እንጂ። የጭካኔያቸው ምንጭ ደግሞ በራሳቸው የማይተማመኑ ደካሞች መሆናቸው ነው። እነርሱ ከዛሬ ሠላሳ ዓመት በፊት በመስታወት ውስጥ ያዩትን የራሳቸውን ምሥል ዛሬም መልሰው ያንኑ ምሥል እያዩት ነው። ከሠላሳ ዓመት በኋላም ሊቀየሩ አልቻሉም። ከዚያ ካረጀው ምሥላቸው ላይ ዓይናቸውን ነቅለው ግዜው እና ሁኔታው የፈጠረውን በአካባቢያቸው ያለውን አዲስ ምሥል ለማየት አቅቷቸውል። ስለዚህ ህወሃቶችን ማስወገድ ግድ ነውና ሁሉም በያለበት ለሚመጣው ለውጥ ራሱን ያዘጋጅ፤ የለውጡም አካል ይሁን እንላለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

Saturday, September 6, 2014

በኮ/ል አለበል አማረ የሚመራው የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ “ከግንቦት 7 ጋር አልተዋሃድኩም” አለ

(ፎቶ ከፋይል)
(ፎቶ ከፋይል)
በኢሳት ራድዮና ቲቪ ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ከስልጣናቸው እንደተነሱ የተዘገበላቸው ኮ/ል አለበል አማረ የሚመራው የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ “እየተካሄደ ነው የሚባለው ውህደት ብዙ ችግር ያለበትና ከእውነትም የራቀ ነው” ሲል መግለጫ አወጣ።
(ፎቶ ከፋይል - የአማራ ዲሞክራቲክ ኃይል ጦር ኃይሎች መካከል የተወሰኑት)
(ፎቶ ከፋይል – የአማራ ዲሞክራቲክ ኃይል ጦር ኃይሎች መካከል የተወሰኑት)

በኮ/ል አለበል አበራ እንደሚመራው ንቅናቄው መግለጫ “የተወሰኑ የድርጅታችን ታጋዮች አሁንም በኤርትራ መንግስት እገታ ኤርትራ ይገኛሉ፤ እነዚሁን ታጋዮች የድርጅቱ አካል በማስመሰልና በማስገደድ ኢንተርቪው እንዲሰጡ በማድረግ የሕገ-ወጡ ተግባር ከማድረግ እንዲቆጠቡና የሂደቱንም አፈጻጸም የተቀዋወሙሙ የድርጅታችን የተወሰኑ ሶስት አመራሮችና ሁለት አመራሮችና ሁለት ካድሬዎች በኤርትራ መንግስት እስር ላይ መሆናቸውን የታወቀ በመሆኑ ይኸው አላስፈላጊ ሁኔታ እንዲስተካከል ለኤርትራ መንግስትና ለተባባሪዎቻቸው በጥብቅ ደጋግመን እናሳስባለን” ይላል። ኢሳት “የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ መሪውን ከሃላፊነት ማንሳቱን አስታወቀ” በሚል የሌላኛውን ወገን የአማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ጠቅሶ በዘገበው ዘገባ ላይ “ኮ/ል አለበል አማረ የድርጅቱ መስራችና ሊቀመንበር ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸውን፣ ውጭ አገር ከሄዱም በሁዋላ ድርጀቱን በማጠናከር ከፍተኛ ሚና መጫወታቸውን” ካወሳ በሁዋላ፣ ድርጅቱ መስዋትነት እየከፈለበት ያለው የነጻነት ትግል በቶሎ ግቡን እንዲመታ መሬት ላይ ወርዶ መታገሉ የበለጠ ውጤታማ ያደርገዋል ተብሎ ስላሚታመን በተደጋጋሚ እንዲመጡ ቢነገራቸው ሊመጡ ባለመቻላቸውና አሁን ባለንበት ጊዜ ድርጅቱን ውጭ ሃገር ተቀምጦ መምራት ስለማይቻል ከድርጅቱ ሊ/መንበርነት ወርደው በአባልነት እንዲቀጥሉ በሙሉ ድምጽ ወስነናል ብለዋል።” ሲል መዘገቡን፤ የኮ/ል አለበል ወገን ይህን ዘገባ ተቃውሟል።
ሙሉ መግለጫውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

Tuesday, August 26, 2014

የወያኔን እድሜ ለማሳጠር በአንድነት እንሠራለን (አርበኞች ግንባር – ግንቦት 7 – የአማራ ዲሞክራሲ ኃይሎች ንቅናቄ)

August26/2014
unityበአገራችን ኢትዮጵያ ላይ የተንሰራፋውን ዘረኛና በታኝ ሥርዓት ለመቀየርና ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ለማውረድ በተለያየ ጎራ ተከፍለው የሚታገሉ ድርጅቶች ቁጥር ከምንጊዜውም በላይ እየበረከተ መምጣቱ የጎጠኛውን ቡድን እድሜ በማራዘም ረገድ ጉልህ ሚና መጫወቱ አሌ የማይባል ሀቅ ነው።
ወቅቱ የሚጠይቀውና አገራችንና ሕዝባችን ያሉበትን ደረጃ በአንክሮ የተረዳ አገርና ሕዝቡን አፍቃሪ የሆነ ድርጅትም ሆነ ቡድን ቆም ብሎ ሊያስብ የሚገባበት ደረጃ ላይ መድረሳችንን የሚያሳይ ነው።
በመሆኑም ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ካሉበት አዘቅት በማውጣት ሕዝቡ የስልጣን ባለቤት የሚሆንበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የጋራ ትግልና መስዋዕትነት የግድ የሚለን ደረጃ ላይ መድረሳንን፤ የወያኔን ቡድን በሁለገብ ትግል እየተፋለምን ያለን ድርጅቶች ተጣምሮና አንድ ሆኖ መታገል እንዳለብን ካመንን ዓመታት አስቆጥረናል።
በአሁኑ ወቅት ከላይ የጠቀስናቸው ሂደቶች ምላሽ አግኝተው አገራችንና ሕዝባችንን ከአዘቅት ለማውጣት በመጣመር ብቻ ሳይሆን በውህደት አንድ ሆነን አገራችንንና ሕዝባችንን አንድ በማድረጉ ረገድ አስፈላጊው መስዋዕትነት በመክፈል የትግል እድሜ እናሳጥር በሚል ለውህደት የሚያደርሰንን ውይይት ለመጀመር የሚያስችል ሂደቶችን አጠናቀን ወሳኝ ወደሆነው ሂደት ውስጥ መግባታችንን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብና ወዳጆች ማብሰር እንፈልጋለን።
ወደፊት ለመዋሃድ የተስማማነው ድርጅቶች
1. የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር
2. የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ
3. የአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ
ስንሆን በሚኖረው የሽግግር ሂደት ወቅትም በሁሉም የትግል ዘርፍ በጋራ መሥራት የጀመርን መሆናችንን እየገለጽን የመላው ወገናችን ድጋፉ እንዳይለየን ስንል ጥሪዓችንን እናስተላልፋለን።
አንድነት ኃይል ነው !!!
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር — የግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ — የአማራ ዲሞክራሲ ኃይሎች ንቅናቄ

ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

August26/2014
Prof. Mesfin Woldemariamጉልበት አራዊት የሚተዳደሩበት ሕግ ነው፤ ሕገ አራዊት የሚባለው አራዊት የሚተዳደሩበት ጉልበት ነው፤ በአራዊት ዓለም ማናቸውም ነገር በጉልበት ያልቃል፤ በሰዎችም መሀከል ጉልበት አድራጊ-ፈጣሪ ሆኖ ጎልቶ ሲወጣ የአእምሮንና የኅሊናን መዳከም ወይም ጭራሹኑ አለመኖር ያመለክታል፤ ጉልበት አለን በማለት፣ ወይም ተመችቶናል በማለት፣ ወይም ጠያቂ የለብንም በማለት የማንኛውንም ሰው ሰብአዊ መብቱንና ሰብአዊ ክብሩን መግፈፍ ሦስት ነገሮችን ያመለክታል፤ አንደኛ ጉልበት እንጂ አእምሮና ኅሊና እንደሌለ፣ ሁለተኛ ጉልበት እንጂ ሕግ እንደማይከበር፣ ሦስተኛ በአንተ ላይ እንዲያደርጉብህ የማትፈልገውን አንተም በሰዎች ላይ አታድርግ የሚለውን ሕግ መጣስን ያሳያል፤ በመጨረሻም፣ ዘግይቶም ቢሆን በራስ ላይ ቅሌትን መጋበዝን ያስከትላል፤ የሌላውን ሰውነት ስናረክስ ሰውነትን በጠቅላላው ማርከሳችን ነው፤ ሰውነትን በጠቅላላው ስናረክስ ራሳችንን ከነጉልበታችን ማርከሳችን ነው፤ ራሳችንን፣ ሰውነታችንን ካረከስን በኋላ ዋጋ የለንም፤ ለራሳችን ዋጋ ከሌለን ለሌለች ሰዎችም ዋጋ አንሰጥም፤ ያኔ ክፉ በሽታ ይይዘናል፤ እግራችን ስር በወደቀ ሰው ስቃይ የምንደሰትና የምንስቅ፣ የምንፈነድቅ እንሆናለን፤ ያን ጊዜ የለየለት በሽተኛ ሆነናል።
ይሄ በሽታ ያቃዣል፤ ከሰው ሁሉ በላይ ያሉ ያስመስላል፤ አግሩ ስር የወደቀው አንድ ሰው የሰው ልጅ በሙሉ ይመስለዋል፤ በሽተኛነቱን ስለማያውቅ በሽታው ከሰው በላይ ያደረገው ይመስለዋል፤ እንዲህ ዓይነቱ በሽተኛ በሕግ አሰከባሪነት ሥራ ውስጥ ሲገባ ሕግ የአንድ ማኅበረሰብ ትምክህትና መከታ በመሆን ፋንታ የበሽተኞች በትር ይሆናል፤ በደርግ ዘመን የአራት ኪሎው ግርማ የሠራውን እናውቃለን፤ ዛሬ ደግሞ ልዩ ግርማዎች አሉ፤ መልካቸውን ከካሜራው ጀርባ ደብቀው በሰው ስቃይና አበሳ በሳቅ እየተንከተከቱ ጀብዱዋቸውን በቴሌቪዥን የሚደረድሩ ጀግኖች መጥተዋል፤ መሣሪያ ይዞ መሣሪያ ባልያዘ ሰው ላይ ጀግና መስሎ ለመታየት የሚሠራው ጨዋታ ራስን ክፉኛ ከማጋለጥ በቀር ሌላ ፋይዳ የለውም።
በኢትዮጵያዊ ሰውነት ላይ ማናቸውንም ከሕግና ከሰብአዊነት ውጭ የሆነ ሙከራ ለማድረግ የውጭ አገር ሰዎች ዕድሉን ይፈልጉት ይሆናል፤ ለነሱ ሰዎች ስላልሆን ሰብአዊነት አይሰማቸውም፤ ከአገራቸው ሕግም ውጭ በመሆናቸው በሕግ አይገዙም፤ ዋናው ውጤት ግን ለኢትዮጵያ ሕግ አስከባሪዎች የሚያስተምሩት ግዴለሽነት ነው፤ መታሰር በብዙ ምክንያቶች ይመጣል፤ ስለዚህ በሠለጠነው ዓለም የተለያዩ እስረኞች በተለያየ ሁኔታ ይጠበቃሉ፤ አንዳንዶቹ እንዲያውም በቤታቸው ውስጥ እየተጠበቁ ይቆያሉ፤ ኢትዮጵያ በራስዋ ሥልጣኔ በምትተዳደርበት ዘመን መሳፍንትና መኳንንት የሚታሰሩት በወርቅ ወይም በብር ሰንሰለት ነበር፤ ግዞትም፣ የቁም እስርም ነበር፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ እስረኞች ሁሉ እኩል ናቸው፤ በቃሊቲ ለየት ያለ አያያዝ የሚታየው ለሙስና ወንጀል ተጠርጣሪዎች ብቻ ነው።
ጉልበትን በጉልበት እቋቋማለሁ የሚል ሰው ሲሸነፍ አያስደንቅም፤ አዲስም አይደለም፤ በአለፉት አርባ ዓመታት እየተሸነፉ ከትግሉ ሜዳ ወጥተው በተለያዩ የምዕራባውያን አገሮች የሙጢኝ ብለው የተቀመጡ አሉ፤ በተባበሩት መንግሥታት ደንብ የሙጢኝ ማለት መብት ነው፤ ይህንን መብት መጣስ የመንግሥተ ሰማያትን በር መድፈር ነው፤ በጎንደር የአደባባይ ኢየሱስን ቤተ ክርስቲያን በር መድፈር ነው፤ በአዲስ አበባ የቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን በር መድፈር ነው፤ በአዲስ አበባ የአንዋር መስጊድን በር መድፈር ነው፤ ወደመሬት ስንወርድም የሙጢኝ የተባለው አገርን መንግሥት መድፈር ነው፤ የተባበሩት መንግሥታት ደንብን መጣስ ነው፤ ለነገሩ የመንግሥተ ሰማያትን በር መድፈር ከተቻለ ሌላው ምን ያቅታል!
የሙጢኝ ያለን ሰው በአፈና መያዝና ወደአገር ማስገባት አንድ ችግር ነው፤ ይህ የጉልበተኛነት መገለጫው ነው፤ ሁለተኛው ችግር የተያዘው ሰው መብቱና ክብሩ ሳይጓደልበት ማስረጃዎችን ሰብስቦ ለነጻ ፍርድ ቤት አለማቅረቡ ነው፤ በቴሌቪዥን እንደታየው አካላዊ ጉዳት እንደደረሰበት ባይታወቅም፣ ጥልቅ መንፈሳዊ ጉዳት እንደደረሰበት ይታያል፤ በብዙ አገሮች ሕጎች አንድ ሰው ራሱን እንዲወነጅል አይገደድም፤ ሕጋዊ ምርመራም በቴሌቪዥን በአደባባይ አይካሄድም።
ስለዚህም በተጠርጣሪው ላይ የተደረገው ሁሉ ሕጋዊ አይደለም፤ በነጻ ፍርድ ቤት ቢቀርብም በቴሌቪዥን የተናገረው ሁሉ ቢያስታውሰውም በማስረጃነት የሚያገለግል አይመስለኝም፤ ስለዚህም ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል።
ከአፍሪካ አህጉር ወጥቶ የቀይ ባሕርን አቋርጦ አንድ ሰው፣ ገና ወደፊት ክፉ ሊሠራ ይችላል በሚል ሂሳብ በጉልበት አፍኖ ማምጣት የብዙ ነፍሶች ዕዳን ተሸክመው በኢጣልያ ኤምባሲ የሙጢኝ ብለው ተደላድለው የተቀመጡትን የደርግ አባሎች ማስታወስ ግዴታ ይሆናል፤ አድርጋችኋል የተባሉትን ሰዎች የሙጢኝ የማለት መብት አክብሮ አስበሃል የተባለውን ሰው የሙጢኝ የማለት መብት መጣስ ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል።
ከፖሊቲካና ከምናምኑ፣ ጉልበተኛነትንም ከማረጋገጡ በላይ ሌላ ትልቅ ነገር አለ፤ አገር የሚባል ነገር አለ፤ ይህ በአንድ ግለሰብ ላይ የተገኘ ጊዜያዊ ድል የአገርን ከብር የሚያጎድፍና የሚያቀል ይሆናል፤ የአንድ አገርን የመንግሥት ሥልጣን የያዘ አካል አንድ ግለሰብን በአደባባይ ከሕግ ውጭ ለማጥቃት ሲሞክር የራሱን ክብር ዝቅ ያደረግበታል፤ ስለዚህም ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል።
በእኔ ዕድሜ ሰው በአደባባይ ሲገረፍ አይቻለሁ፤ ሰው ተሰቅሎ አይቻለሁ፤ የዚያን ዘመን የእውቀት ደረጃ የዚያን ዘመን የሰው ልጆች የመንፈስ እድገት ደረጃ ያመለክታል፤ የእውቀትም የመንፈስም ደረጃ በጣም ዝቅተኛ ነበረ ማለት ነው፤ ስለዚህም ይህንን ያደረጉትን ዛሬ አንወቅሳቸውም ይሆናል፤ የታሪካችን ጉድፍ መሆኑን ግን ልንፍቀው አንችልም፤ ስለዚህም ሌላ ጉድፍ እየጨመርንበት ታሪካችንን ማቆሸሹ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ይበልጣል።
ቅጣት በሕግና በሥርዓት ይደረግ ማለት ያጠፋ ሰው አይቀጣ ማለት አይደለም፤ ነገር ግን ምንም አቅም የሌለውን ሰው ይዞ በአደባባይ ማሰቃየትና ማዋረድ አገርንና ሕዝብን ማዋረድ ነው፤ የሰብአዊነትንም የሕጋዊነትንም ሚዛኖች ይሰባብራል።
ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ሐምሌ 2006

Monday, August 25, 2014

አርበኞች ግንባር፣ ግንቦት 7 እና የአዲሃን ወደውህደት የሚያደርሳቸውን ውይይት ሊጀምሩ ነው

(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር፣ ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እንዲሁም የአማራ ዲሞክራሲ ሃይሎች ንቅናቄ ወደ ውህደት የሚያደርሳቸውን ውይይት ሊጀምሩ መሆኑን ለዘ-ሐበሻ በላኩት መግለጫ አስታወቁ።
“የወያኔውን ዕድሜ ለማሳጠር በአንድነት እንሰራለን” በሚል ድርጅቶቹ በጋራ ባወጡት መግለጫ “ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ካሉባት አዘቅት በማውጣት ሕዝቡ የስልጣን ባለቤት የሚሆንበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የጋራ ትግልና መስዋዕትነት የግድ የሚለን ድረጃ መድረሳችንን የወያኔውን ቡድን ነፍጥ አንስተን እየተፋለምን ያለን ድርጅቶች ተጣንሪባ አንድ ሆኖ መታገል እንዳለብን ካመንን አመታትን አስቆጥረናል” ብለዋል።
ሙሉ መግለጫው የሚከተለው ነው፦
arbegnoch ginbar and ginbot 7

የኢሳት ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና እህት የግፍ ሰለባዋ

August25/2014
10645174_704513272957683_171991983121885364_n አስቂኝና ጥርስ የማታስከድን ወጣት ናት። ከእሷ ጋር ለደቂቃ አይደለም ለሰዓታት አብረህ ብታሳልፍ አይሰለችህም፤ በሳቅ ታንከተክትሃለች። አነጋገሯ ፈጠን..ፈጠን ያለ ነው። ..የሷ ቀልዶች አይረሱኝም።..በ1998 ዓ.ም የደረሰባት ነገር እጅግ አሳዛኝ ነው። የተቃዋሚ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ የቅንጅት ደጋፊዎችና ሰላማዊ ዜጎች በጅምላ እስር ቤት ሲጋዙ አጋጣሚ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ለሁለት ወር ገደማ እጁን ሳይሰጥ ተሰውሮ ነበር። የገዢው ባለስልጣናት (በረከትና መለስ ናቸው) ያሰማሯቸው ደህንነቶች ሲሳይን ፍለጋ ብዙ ሲማስኑ ነበር። ያላሰሱትና ያልተከታተሉት ሰው የለም፤ በመጨረሻ ግን እህቱን አፈኑ። እየደበደቡ ወደ ወለጋ ወሰዷት። ሴት ልጅ ልትቋቋመው ከምትችለው በላይ በዱላ አሰቃይዋት። « ሲሳይ የት ነው ያለው? ተናገሪ?» ሲሉ ፍዳዋን አስቆጠሯት። ምንም እንደማትውቅ ነገረቻቸው። ምንም ሲያጡ ወለጋ ላይ ፀጉሯን ላጭተው፣ በድብደባ ጐድተውና አቁስለው፣ እጅግ አዳክመው ጫካ ውስጥ አውሬ እንዲበላት ጥለዋት ሄዱ። ራሷን የሳተችው አቦነሽ (ቴሌ) ፈጣሪ ነፍስሽ ይትረፍ ሲላት ገበሬዎች አገኟት። ተሸክመው ወሰዷት። በመኖሪያ ጐጆዋቸው እንድታገግም አደረጉ። ከዚያም ስልክ ወደ አዲስ አበባ አስደወሉላት። ጋዜጠኞች ስፍራው ድረስ ሄደው አመጧት። ..እነሆ ከ8 ዓመት በኋላ ሌላ ክስ ከሙያ ባልደረቦችዋ ጋር ተመሰረተባትና በዚህ ሰሞን አገር ጥላ ተሰደደች። ይህ ግፍ መቆሚያው የት ይሆን!?…ስለተሰደዱት ጋዜጠኞች እመለስበታለሁ።
(በፎቶው የሲሳይ አጌና እህት በመሆኗ ብቻ በ1998ዓ.ም የተፈጸመባት ግፍ ይህን ይመስላል)

Thursday, August 21, 2014

ከወያኔ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስልጠናዎች የተረዳነው:- ወጣቱ ለለውጥ ዝግጁ ነው፤ የቀረው ድርጅት ነው

August21/2014
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተመሠረቱበት ዓላማ የእውቀትና ጥበብ መበልፀጊያና ማስፋፊያ እና የምርምር ማዕከላት እንዲሆኑ ነው። እውቀትና ጥበብ እንዲበለፅጉ እና የምርምር ሥራዎች እንዲዳብሩ የአካዳሚ ነፃነት መኖሩ ቁልፍ ጉዳይ ነው። የአካዳሚ ነፃነት ሳይኖር መምህራኑም ተማሪዎቹም በነፃነት ማሰብ፣ አስቸጋሪ ጥያቄዎችን ማንሳት እና ለጥያቄዎቻቸው መልስ ለመሻት መመራመር አይችሉም። የአካዳሚ ነፃነት ሳይኖር የተለያዩ እይታዎችንና ንድፈሀሳቦችን በገለልተኛነትና በሀቀኝነት መመርመር አይቻልም። በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የአካዳሚ ነፃነት እንዲኖር ተቋማቱ ከፓርቲ ፓለቲካ ገለልተኛ መሆን ይኖርባቸዋል። አንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የአንድ ፓርቲ ርዕዮተ ዓለም አራማጅ ከሆነ ተቋሙ የፓርቲው ካድሬዎች ማሰልጠኛ ሆነ ማለት ነው። ዛሬ በአገራችን የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙበት ሁኔታ ይህ ነው። የአገራችን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የወያኔ ካድሬዎች ማሰልጠኛ ሆነዋል። ይህ አጅግ አሳሳቢ ጉዳይ ነው።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወደ ህወሓት ካድሬ ማሰልጠኛነት መዝቀጥ አንድ ተጨባጭ ማስረጃ ሰሞኑን ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በፕላዝማ ቴሌቪዥን አማካይነት በመሰጠት ላይ ያለው ፕሮፖጋንዳ ነው። በዚህ ፕሮፖጋንዳ ያልተጠመቀ ተማሪ የሚቀጥለው ዓመት መደበኛ ትምህርት አይቀጥልም በማለት ተቋማቱ ለካድሬ ማሰልጠኛነታቸው እውቅና ሰጥተዋል።
በዚህ ብዙ የአገር ሀብትና ጊዜ በፈሰሰበት ቅስቀሳ፣ የወያኔ ካድሬዎች ዘረኛና ከፋፋይ ፓሊሲዎቻቸውን ማር ቀብተው ወጣቱን ለመጋት እየጣሩ ነው። ለፓርቲ ቅስቀሳ የመንግሥትን መዋቅር መጠቀም በራሱ ወንጀል ቢሆንም ከዚህ በላይ ጉዳት ያለው ደግሞ የፕሮፖጋንዳው ይዘትና ዓላማ ነው። ወያኔ/ኢሕአዴግ ሁሉንም ነገር የሚያውቅ፤ ሁሉንም ነገር ማድረግ የሚችል ተደርጎ የተዘጋጀው ፕሮፖጋንዳ በትውልድ ላይ የሚያስከትለው የእውቀትና የሥነ ልቦና ኪሳራ ከፍተኛ ነው።
በዚህ “ስልጠና” ተብሎ በሚሞካሸው ርካሽ ፕሮፖጋንዳ አማካይነት አድርባይ የሆነው ወያኔ ወጣቱን ለአድርባይነት እያዘጋጀው ነው። የወያኔ ዓላማ የኢትዮጵያ ወጣት መስሎና ዋሽቶ አዳሪ እንዲሆን ማድረግ ነው። የስልጠናው ዓላማ ወጣቶች ለግል ሕወታቸው ምቾች ሲሉ የወያኔ አባላትና ደጋፊዎች እንዲሆኑ ማድረግ ነው። የስልጠናው ዓላማ “ወይን ለኑሮ” ተቀባይነት ያለው የኑሮ ዘይቤ ለማድረግ ነው። ይህ ደግሞ የከፍተኛ ትምህርትን መሠረተ ሀሳብን ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነት ነፃነት-ወዳድ ባህልንም የሚፃረር ነው። በዚህም ምክንያት ወያኔ የወጣቱን ትውልድ ላይ አዕምሮ ለማላሸቅ የሚነዛውን ፕሮፖጋዳ መቃወም የኢትዮጵያዊያን ሁሉ የዜግነት ግዴታ ነው።
ደግነቱ በአብዛኛዎቹ የስልጠና አዳራሾች እየሆነ ያለው ወያኔ ያሰበውና የተመኘውን አይደለም። የኢትዮጵያ ወጣት የወያኔን ዘረኛ ፕሮፖጋንዳ የሚጋት እንዳልሆነ እያስመሰከረ ነው። በብዙ አዳራሾች የወያኔ ካድሬዎች ሊመልሷቸው ከማይችሏቸው ጥያቄዎች ጋር ተፋጠው እንዲያፍሩ ተደርገዋል። ወጣቶች፣ “የታለ የምታወሩለት እድገት ?” “ቻይና በሠራው እናንተ የምትፎክሩት ለምንድነው?“ “ፍትህ የት አለ?” “የአንድ ብሔር የበላይነትን ነው እኩልነት የምትሉት?” እያለ ካድሬዎችን እያፋጠጠ ነው። ወጣቱ አፈና በበዛበት ሁኔታ ውስጥም ሆኖ መሠረታዊ የሆኑ ጥያቄዎችን ለማንሳት መድፈሩ፤ በአንዳንድ አዳራሾች ደግሞ በጩኸት የፕሮፖጋንዳውን ሥራ ማወኩ ወጣቱን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዊያንን ሁሉ የሚያኮራ ተግባር ነው።
ወያኔ፣ ወጣቱን አድርባይነትን ለማስተማር ያዘጋጀው ስልጠና የወጣቱ ቆራጥነትና አርበኝነት ማሳያ ሲሆን፤ ፍርሃት ለማስፈን የተጠራ ስብሰባ ድፍረትን አደባባይ ሲያወጣ ማየት የሚያኮራ ነው። ወጣቱ በዚህ ስልጠና ላይ ባሳየው ድፍረት ለለውጥ ምን ያህል ዝግጁ እንደሆነ አሳይቷል። አሁን የጎደለው ድርጅት ነው። የወጣቱ ለለውጥ ዝግጁ መሆን አንድ ትልቅ የምሥራች ነው። ይህ ዝግጁነት በድርጅት መደገፍ ደግሞ ተከታትሎ መምጣት ያለበት ሥራ ነው። የወጣቱ የመንፈስ ዝግጅትና ድርጅት ከተቀናጁ የወያኔ ውድቀት ቅርብ ነው።
ወጣቱ ከተቃውሞ ባለፈ ሊሠራቸው የሚገቡ በርካታ ጉዳዮች ከፊቱ ተደቅነዋል። ከሁሉ አስቀድሞ ድርጅት ወሳኝ ጉዳይ እንደሆነ ሊጤን ይገባዋል። ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በወያኔ አገዛዝ ሥር ባለችው ኢትዮጵያ ውስጥ ምስጢራዊና ማዕከላዊነትን ያልጠበቁ ትናንሽ ስብስቦች ይበልጥ ውጤታማ ይሆናሉ ብሎ ያምናል። ስለሆነም ግንቦት 7፣ እያንዳንዱ ለሀገሩ፣ ለነፃነቱ፣ ለክብሩ፣ ለፍትህ ግድ ያለው ወጣት ከሚመስሉትና ከሚያምናቸው ጥቂት ወዳጆቹ ጋር በምስጢር እንዲደራጅ አጥብቆ ይመክራል። የተደራጁ ስብስቦች ግንቦት 7ን ማግኘት ወይም ግንቦት 7 እነዚህን ስብስቦች ማግኘት አስቸጋሪ አይሆንም። የኢትዮጵያ ወጣት ለለውጥ ዝግጁ ነው። የጎደለው ድርጅት ነው። የጎደለውን ማሟላት ደግሞ የሁላችንም ግዴታ ነው።
ግንቦት 7:የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በወያኔ ስልጠናዎች ላይ ተቃውሞ ለማሰማት በመድፈራቸው የተሰማውን ደስታ ይገልፃል። ይህ ክስተት ወጣቱ ለለውጥ የተዘጋጀ እንደሆነ በአመላካችነት ወስዶታል። ይህ የለውጥ ፍላጎት በድርጅት ካልታገዘ ውጤት ስለማያመጣ ወጣቱ በትናንሽ ሕዋሶች ራሱን እንዲያደራጅ ይመክራል። ይህንን ካደረግን የወያኔ ፋሺስታዊ አገዛዝን የምናስወግድበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

አብርሃ ደስታ ሃብታሙ አያሌዉና እና ኤርትራ

August21/2014
( ግርማ ካሳ)

ራሱን ግንቦት 7 ብሎ ከሚጠራ ድርጅት ጋር እና ከድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች በመገናኘት ፤ እንዲሁም ከባንክ በትዕዛዝ ብር በመቀበል የግንቦት 7 ተልዕኮና አላማ ለመፈፀም፤ ቁጥራቸው ከ60 በላይ የሆኑ ግለሰቦችን ለዚህ ጥፋት እንዲሰማሩ በማድረግ» የሚል ክስ ነው በወዲ ሃዉዜን/ትግራይ በሆነው አንጋፋ ፖለቲከኛ እና ብሎገር ላይ ክስ የቀረበው። ሌላው አንጋፋና አንደበተ ርትኡ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ ግብረ ኃይል ሰብሳቢ፣ ሃብታሙ አያሌውም፣ «የግንቦት ሰባት ተባባሪ ነው» በሚል ነው ለመክሰስ ነው ዝግጅት እየተደረገ ያለው።

አብርሃ ደስታ እና ሃብታሙ አያሌው ፣ «ግንቦት ሰባትን ይደግፋሉ» የሚል ክስ ከቀረበባቸው፣ በተዘዋዋሪ መንገድ «ከሻእቢያ ጋር ወዳጆች ናቸው» ማለት ነው። ታዲያ የሻእቢያ ወዳጅ የሆነ ሰው፣ የኤርትራን መገንጠል ተቃዉሞ፣ ወይንም የኢትዮጵያን የባህር በር ባለቤት መከበር እንዳለበት በማስመር ይናገራል ወይ ? እስቲ የጸረ-ሽብርና የአገር ደህንነት ተብዬው ምላሽ ይስጠን !!!
ሁላችንም እንደምናውቀው፣ በኤርትራ በኩል ትግል እናደርጋለን የሚሉ ወገኖች፣ ኢትዮጵያ የባህር በር እንደሚያስፈልጋት ሊናገሩ አይችሉም። በሻእቢያ ሥር እስካሉ ድረስ ቀይ መስመር ተሰምሮላቸዋል። እነ ግንቦት ሰባቶች፣ ኦነጎች ...፣ እርዳታ የሚያገኙጥ ከሻእቢያ ማእከላቼ ደግሞ አስመራ እስከሆነ ድረስ፣ «ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል» ብለው የመናገራቸው ነገር ጭራሽ የማይታሰብ ነው።

ዶር ብርሃኑ ነጋ ከቃሊት እሥር ቤት ሆነው የጻፉት አንድ መጽሃፍ ነበር። መጽሀፍ ላይ ባለው የ ኤርትራ ካርታ ፣ ኤርትራ ተቆርጣለች። ሃብታሙ አያሌው የጻፈው መጽሃፍ ላይ በሚታየው የ ኤርትር ካርታ ኤርትራ አልተቆረጠችም። ሃብታሙ አያሌው፣ ምንም እንኳን ሻእቢያና ሕወሃት/ኢሕአዴግ ከመረብ በስተሰሜን እና በስተደቡብ ያለዉን ሕዝብ ከፋፍለው፣ በደም ቢያቃቡትም፣ «ሰላማዊ በሆነ መንገድ፣ ሁለቱም ወገኖች አሸናፊ በሆኑበት መልኩ፣ 

ወንድማማቾችን አንድ ይቻላል» የሚል እምነት ስላለው ነው፣ ኤርትራ ከተቀረው የኢትዮጵያ አካል ጋር የቀላቀላት። ከ23 አመታት በፊት ያለው አስቦ ሳይሆን ፣ ወደፊት የሚሆነው ታይቶት ነው። ታዲያ ይህ አይነት ፖለቲከኛ ነው የሻእቢያ አሽከር ነው ተብሎ የሚከሰሰው ?
ወደ አብርሃ ደስታ ልውሰዳችሁ። በቅርብ ጊዜ ስለ አሰብ የጻፈው አስደናቂ ጽሁፍ ነበር።

 «ጦርነት ፈርተን ግን ሐገራችንን አሳልፈን አንሰጥም» በሚል ርእስ፣ በአደብ ጉዳይ ላይ፣ አብርሃ ደስታ ሲጸፍ « እኛ ጦርነት አንፈልግም። ሕጋዊ ንብረታችን (ወደባችን) በሰለማዊ መንገድ እንዲሰጠን ነው የምንጠይቀው። አዎ! ጦርነት አንፈልግም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ግን ጦርነት ከፍተን በሃይል የሌላ ሀገርና ህዝብ ንብረት አንወርም ማለት እንጂ ጦርነት ፈርተን ልአላዊ ግዛታችን (ሃብታችን) ለሌሎች ሃይሎች አሳልፈን እንሰጣለን ማለት አይደለም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ጦርነት እንፈራለን ማለት አይደለም። አዎ! ጦርነት ስለማንፈልግ ሌሎች ህዝቦችን አንወርም። ጦርነት ፈርተን ግን እናት ሀገራችን አናስደፍርም» ነበር ያለው።

ታዲያ በምን መሰፍርትና ሚዛን ነው አቶ ሃብታሙ አያሌው እና አቶ አብርሃ ደስታ የ«ሻእቢያ ተላላኪ» የሚሆኑት ? በምን መስፈርት ነው ግንቦት ሰባቶች ሊባሉ የቻሉት ?
«ህወሓት በራሱ ኮ የሻዕቢያ ተልእኮ ለማስፈፀም በሻዕቢያ የተቋቋመ ድርጅት ነው። ህወሓት የመሰረተው ማነው? ሻዕቢያ ነው። ሻዕቢያ መሓሪ ተኽለ (ሙሴ) የተባለ ኤርትራዊ የሻዕቢያ አባል በትግራይ ለሻዕቢያ ሊያግዝ የሚችል ድርጅት እንዲያቋቁም ወደ ኢትዮዽያ ላከ። እነዚህ ህወሓት የመሰረቱ የሚባሉ ሰባት ሰዎች አሰባስቦ እንዲደራጁ አደረገ» ብሎ አብርሃ ደስታ እንደጻፈው፣ ለሻእቢያ ዉስጥ ዉስጡን የሚቆረቀረዉስ ሕወሃት አይደለችንም ? ያ ባይሆን ኖሮ ተሽቀዳድሞ የአልጀርስ ስምምነት ይፈረም ነበርን? ያ ባይሆን ኖሮ አገር ቤት ካሉ ሰላማዊ ተቃዋሚዎች ጋር አልነጋገርም እያሉ፣ የሕወሃት/ኢሕአዴጉ ዳግማዊ መለስ ዜናዊ፣ ኃይለማሪያም ደሳለኝ «ካስፈለገም አስመራ ድረስ እሄዳለሁ» ይሉ ነበርን ?

እርግጥ ነው እነዚህ ሁለቱ አንጋፋ ወጣት ፖለቲከኞች፣ ኢሳት በተሰኘው ሜዲያ ቀርበው ቃለ ምልልስ አድርገዋል። አቦይ ስብሐት ነጋ፣ አምባሳደር ቪኪ ሃደልሰን፣ ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን፣ ወንጌላዊ ዳንኤል ጣሰው ..የመሳሰሉትም በኢሳት ቀርበዋል። ታዲያ እነ አባይ ስብሐት ፣ «ኢሳት ላይ ቀረባችሁ» ተብለው ወደ ወህኒ የወረዱበት ሁኔታስ የታለ ?

በአንድ ሜዲያ መቅረብ አንድን ሰው ጥፋተኛ አያሰኘዉም። አንድ ሰው መከሰስ ካለበት፣ ሊከሰስ የሚገባው በቃለ መጠይቆቹ ዉስጥ ባለው ይዘት ነው። አቶ ሃብታሙና አቶ አብርሃ፣ ሲጽፉም ሲናገሩም በግልጽና በአደባባይ እንደመሆኑ «ይሄን ተናገረዋል.. » ተብለው የሚከሰሱበት ነጥብ ይኖራል ብዬ አላስብም። በመሆኑም አገዛዙ ፣ እነዚህ ሰላማዊ ዜጎችን ሽብርተኞች ናቸው ብሎ ማሰሩ የትም አያደርሰውም። ይህ አይነቱ ፍርድ ገምድልነትና ዜጎችን ያለ ከልካይ ማሰርና ማንገላታት መቆም አለበት።

መለስን ቅበሩት!(ተመስገን ደሳለኝ)

August 21, 2014

ከኢትዮጵያ ሀገሬ የደቀቀ ኢኮኖሚ ላይ በማን አህሎኝነት ወጪ ተደርጎ፣ ቅጥ ባጣ መልኩ በመላ አገሪቱ እየተከበረ ስላለው የቀድሞ አምባገነን ጠ/ሚኒስትር ሁለተኛ ሙት ዓመት ዝክርም ሆነ ሰውየውን ዛሬም በአፀደ-ህይወት ያለ ለማስመሰል እየሞከሩ ላሉት ጓዶቹ አንዲት ምክር ብጤ ጣል ማድረጉ ተገቢ ነው ብዬ ስለማስብ በአዲስ መስመር እንዲህ እላለሁ፡-

አብዮታዊው ገዥ-ግንባር ግንቦት ሃያ፣ የህወሓት ምስረታ፣ የብአዴን አፈጣጠር፣ የኦህዴድና የደኢህዴን ውልደት፣ የብሔር ብሔረሰቦች በዓል፣ የባንዲራ ቀን፣ የመከላከያ ሳምንት፣ የፍትሕ ሳምንት፣ የሕዳሴ ግድብ መሰረት ድንጋይ የተጣለበት… ጅኒ-ቁልቋል እያለ ዓመቱን ሙሉ በማይጨበጥ ተራ ፕሮፓጋንዳ ማሰልቸትን መንግስታዊ ኃላፊነት አድርጎታል፡፡ ይህ እንግዲህ ለቁጥር የሚያታክቱ፣ በነጭ ውሸት የታጨቁ እና በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ቅኝት የተንሸዋረሩ ‹ዶክመንተሪ ፊልሞቹ›ን ረስተንለት ነው፡፡

ይህ ሁሉ ያልበቃው ‹‹ጀግናው›› ኢህአዴግ ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ህልፈት ወዲህ፣ ወርሃ-ነሐሴንም እንደ ግንቦት ሃያው
ሁሉ የሟቹን ታጋይነትና አብዮታዊነት፤ ሕዝባዊነትና አርቆ አስተዋይነት፤ የርዕዮተ-ዓለም ተራቃቂነትና የአየር ንብረት ተካራካሪነት፤ በፖለቲካ ቢሉ በኢኮኖሚ ቁጥር አንድ ጠቢብነትና ባለራዕይነት፤ ፍፁም ፃድቅነትና ሰማዕትነት…. የሚተረክበት ሲያደርገው ቅንጣት ታህል ሀፍረት አልተሰማውም፡፡ ሰሞኑን በ‹‹ኢትዮጵያ›› ቴሌቪዥን ግድ ሆኖብን ተመልክተንና ሰምተን በትዝብት ካሳለፍናቸው ‹‹መለስ፣ መለስ›› ከሚሉ የከንቱ ውዳሴ አደንቋሪ ድምፆች በተጨማሪ፣ የኦሮሞን ባሕላዊ ልብስ ሲያለብሱት፣ ሐረሪዎች ጋቢ ሲደርቡለት፤ በደቡብ የሚገኙ ብሔሮች የየራሳቸውን ባሕል የሚወክሉ አልባሳት ሲሸልሙት፣ ስለወላይታነቱ ሲመሰክሩለት…

ደጋግመን ለመመልከት ተገደናል፤ ይሁንና ድርጅቱ ስለ ቀድሞ ሊቀ-መንበሩ አልፋና ኦሜጋነት ለመስበክ ዙሪያ ጥምዝ ከዳከረለት ከእንዲህ አይነቱ የተንዛዛ ፕሮፓጋንዳ ይልቅ፣ በዚሁ የቴሌቪዥን መስኮት የቀረበ አንድ ጎልማሳ ‹‹መለስ ሁሉም ማለት ነው›› ሲል የሰጠው አስተያየት፣ ቅልብጭ አድርጎ ይገልፅለት ነበር ብዬ አምናለሁ፡፡ የዚህ አይነቱ ምጥን አስተያየትም በጥራዝ ነጠቅነት ዘላብዶ የኋላ ኋላ በሀፍረት ከማቀርቀር ያድናል፡፡ ለምሳሌ እናንተ የግንባሩ ካድሬዎች ስለመለስ ምሁርነት ለመናገር ስትዳዱ ሁሌ የምትደጋግሙት፣  ያንኑ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ አርቃቂነቱ እና የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ኀልዮት አዋቃሪነቱ ነው፡፡ ግና፣ ይህ ‹‹ንድፈ-ሃሳብ›› ተብዬ ራሱ በርዕዮተ-ዓለምነት ለመጠራት የማይበቃ የተውሸለሸለ ጭብጥ ስለመሆኑ በርካታ ምሁራን በጥናቶቻቸው ከማስረገጣቸው ባሻገር፣ አገሪቷን ለከባድ ኢኮኖሚያዊ ድቀት፣ ሕዝቧን ደግሞ ለጥልቅ ድህነት መዳረጉን ብቻ ማስታወሱ በቂ ይሆናል፡፡ ስለልማታዊ መንግስት አዋጭነት በብቸኝነት እንደተከራከረ ተደርጎ የሚለፈፈውን እንኳን ንቆ መተው ሳይሻል አይቀርም፡፡ ከታንዲካ ማካንደዋሬና መሰል የፅንሰ-ሃሳቡ አበጂዎች የዘረፋቸውን መከራከሪያዎች ማን ዘርዝሮ ይዘልቀውና፡፡ ‹መለስን ቅበሩት› የምለውም፣ እንዲህ ያሉ አስነዋሪ ማንነቶቹን ማስታወስ ስለሚያም ነው፡፡

እናም እውነት እውነት እላችኋለሁ፡- ስለሰውዬው የምትነግሩን እና የምታስቀጥሉት ‹ሌጋሲ›ም ሆነ የምትተገብሩት ረብ ያለው አንድም ራዕይ የለምና ዝም፣ ፀጥ ብላችሁ የምራችሁን ቅበሩት፡፡ እስቲ! ኦጋዴንን ተመልከቱ፤ ካሻችሁም ወደ አኝዋኮች ተሻገሩ፤ ያን ጊዜ እናንተ በአርያም የሰቀላችሁት ሰው፣ ለነዚህ ሁለት ብሔሮች የቀትር ደም የጠማው ጨካኝ መሪ እንደነበር፣ በክፋት ትዕዛዞቹ ጥፋት ከተረፈ ጠባሳ ትረዱታላችሁ፡፡ ለአቅመ-ሔዋን ያልደረሱ ህፃናት በሰልፍ የሚደፈሩባት፣ ወጣቶች እንጀራ ፍለጋ በተስፋ-ቢስነት ጥልቁን ውቅያኖስ ሰንጥቀው ለመሰደድ የማያመነቱባት፣ የጤና ኬላ ማግኘት ተስኗቸው በልምሻ የሚባትቱ ብላቴኖችን በአቅም-የለሽነትና በቁጭት የምናስተውልባት ደካማ አገር አስረክቦን እንዳለፈ ከወዴት ተሰወረባችሁ? ከቀዬዎቻቸው በጉልበት ለተፈናቀሉ ወገኖች በመቆርቆር ‹‹ሕግ ይከበር!›› ባሉ በየጉራንጉሩ ወድቀው እንዲቀሩ የተፈረደባቸው ጎበዛዝትን ሬሳ እንድንቆጠር ያደረገን ደመ-ቀዝቃዛ ‹መሪ› እንደነበረስ ስንት ጊዜ እያስታወስን እንቆዝም? ቀደምት አባቶች ወራሪውን ፋሽስት ለማንበርከክ የተዋደቁባቸው ጢሻና ኮረብቶች በዚህ ዘመን የዜጎች ወደሞት አገራት መሸጋገሪያ ጽልማሞቶች የሆኑት በማን ሆነና ነው? ከሕግ ተጠያቂነት ቢያመልጥ፣ ከታሪክ ተወቃሽነት ልትታደጉት የምትችሉ ይመስላችኋልን?

…ይልቅ እመኑኝ! ፀጥ ብላችሁ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ጥልቅ ጉድጓድ ቆፍራችሁ ቅበሩት! ላይመለስ በመሄዱም እንደ ግልግል ቆጥራችሁት እርሱት!! መቼም በገዛ ራሱ ሕዝብ ላይ ትውልዶች ይቅር ሊሉት የሚሳናቸውን ይህን መሰሉ መከራ ላዘነበ ሰው በአፀደ-ስጋ ሳለም ሆነ በበድን የሙት መንፈሱ ስር በየዓመቱ ለአምላኪነት መንበርከክ፣ የናንተን አልቦ ማንነት እንጂ ሌላ አንዳች የሚነገረን ቁም ነገር ጠብ ሊለው አይችልም፡፡ ይህም ሆኖ ለመለስ አምልኮ እጅ መስጠት አሳፋሪነቱ፣ ለካዳሚዎቹ ብቻ መሆኑን መስክሮ ማለፉ የቀሪዎቻችን ዕዳ እንደሆነ መገንዘብ አለብን፡፡

Wednesday, August 20, 2014

(Breaking News) 7 ጋዜጠኞች ሃገር ጥለው ተሰደዱ

ጋዜጠኛ ግዛው ታዬጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው
ጋዜጠኛ ግዛው ታዬጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው

(ዘ-ሐበሻ) መንግስት ሰሞኑን በነጻው ፕሬስ አባላት ላይ የጀመረውን ሰዶ የማሳደድ ተግባር ሰለባ የሆኑት 7 ጋዜጠኞች ሃገር ጥለው መውጣታቸውን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው ሰበር ዜና አመለከተ::
ከሰሞኑ በፍትህ ሚ/ር ክስ የተመሰረተባቸው እነዚሁ ጋዜጠኞች የሎሚ መጽሔት, የአፍሮ ታይምስ ጋዜጣና እና የጃኖ መጽሔት አዘጋጆች ሲሆኑ እነርሱም
1ኛ. ጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው
2ኛ. ጋዜጠኛ ዳንኤል ድርሻ
3ኛ. ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ
4ኛ. ጋዜጠኛ አስናቀ ልባዊ
5ኛ. ጋዜጠኛ ሰናይ አባተ
6ኛ. ጋዜጠኛ ሰብለወንጌል መከተ
7ኛ. አቦነሽ
የተባሉ ሲሆን ዝርዝሩን ወደ በሁዋላ ይዘን እንመለሳለን::
-- Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.--





በአንድነት ሃይሎችና በህወሃት መካከል ያለች ስዊንግ ስትቴ ኮሎራዶ! በሮቤል

August 20/2014
በአንድነት ሃይሎችና በህወሃት መካከል ያለች ስዊንግ ስትቴ ኮሎራዶ!

“ወይን ለኑሮ” ተቀባይነት ያለው የኑሮ ዘይቤ እየተባለች የምትጠራዋ ኮሎራዶ በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚኖሩባት ከተማ ብትሆንም  ቅሉ ሁሉም ግን የህወሃት ደጋፊዎች ናቸው ማለት በጣም አስቸጋሪ ነው። ለዚህ ዋቢ ማስረጃ ከትግራይ የወጡ ጠንካራ የአረና ፓርቲ የኮሎራዶ ቻፕተር ተጠቃሽ ነው። አረና በኮሎራዶ ከአንድነት ሃይሎች ጋር ብዙ ጊዜ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ይታያል።

ስለዚህ የጽሁፌ መነሻ በህወሃትና በተቃዋሚዎች መካከል መፈራረቅ የበዛባት ኮሎራዶ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በርካታ እንቅስቃሴዎችን በተቃዋሚው ጎራ እየታየባት ነው። ኮሎራዶ እንኳን ለአበሾቹ፣ ለነጮቹም በዴሞክራቶችና በሪፐብሊካን ያለች ስዊንግ ስቴት(swing state) ነች። ልዩነቱ ለሆዳቸው ባደሩ፣ ለስምና ለዝና ሲሉ ለሃገራቸው ውድቀት ሌት ተቀን በሚሰሩና ሃይሎችና፤ ለእውነተኛ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ በሚታገሉ ነው።

ኮሎራዶ የወያኔ መሪዎች በሰላም ገብተው የሚወጡባት ከተማ ነች። በኮሎራዶ ያለው የህወሃት ስልት በተቃዋሚ ጎራ ያሉትን በ 40/60 እና በሌሎች ጥቅማ ጥቅም በመደለል የገለልተኛ ካርድ በመስጠት ቢያንስ እንቅፋት ለህወሃት እንዳይሆኑ ከፍተኛ መዋእለ ነዋይ በማፍሰስ ቢያንስ (undecided voters) እንዲሆኑ ይሰራል።

ከእነዚህ ውስጥ ተጠቃሾች የእምነት ተቋማትን እርስ በርስ ማጋጨት፣ የኮሚውኒቲ ማህበራትን በየጎራው በመክፈል ለምሳሌ በብሄር የተደራጁ፣ የትግራይ ተወላጆች ኮሚውኒቲ፣ የአፍሪካ ኮሚውኒቲ ሴንተር  እና ዋነኛውና ሌላው የገለልተኛ ካርድ በመምዘዝ ደግሞ የኢትዮጵያ ኮሚውኒቲ በኮሎራዶ  በሚል ተቋማትን ፈጥሮ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በዝርዝር እመለስበታለሁ።

ኮሎራዶ በርካታ ኢትዮጵያኖች የሚገኙባት ተራራማ ከተማ ስትሆን፣ ህወሃት ወያኔ የተመሰረተባት ከተማ በመባልም ትጠቀሳለች፡፡ ከተማዋም አክሱም ሲስተር ሲቲ በሚል የህወሃት ባለስልጣኖች በአክሱም ስም ፓርክ እንዲሰየምላቸውም አድርገዋል። ምንም እንኮን አክሱም የሁላችን ቢሆንም ትልቅ መዋእለ ነዋይ አፍሰዋል። እንግዲህ ይህ በሚሆንባት ከተማ የተቃዋሚ ሃይሉ በጋራ በመሆን ለኢትዮጵያ አንድነት ልዩነትን በማቻቻል እየሰራ ቢሆንም ቅሉ ገና በርካታ ስራዎችን በመስራት ኮሎራዶ እንደ ተቀረው የአሜሪካን ስቴት ወያኔዎች የሚዋረዱባት እና የሚሰቀቁባት ከተማ ለመሆን ግን ሰፊ ስራዎች ያስፈልጋሉ። ኮሚውኒቶችን ማጠናከር፣ እድሮችንና፣ ማህበራዊ ስብሰባዎችን ማደራጀት ያስፈልጋል። በቤተክርሰቲያን ያሉ ልዩነቶችን በሰከነ መፍታትም ተገቢ ነው።

በርግጥ ነው ኢትዮጵያን የገጠማት ፈተና አድረባይነትና “ወይን ለኑሮ” ተቀባይነት የሌለው የዘመኑ የኑሮ ዘይቤ ሲሆን፣ ኮሎራዶም የተቃዋሚ ሃይል ደጋፊ ነው የሚባለው ከህወሃት አባላት ይልቅ የሌላው ብሄር ተወላጅ እራሱን አናሳ በማድረግ ተላላኪነትን ወይም አዲስ አበባ ስገባ በሚል ወያኔዎች ያዘጋጁትን የገለልተኛ መታወቂያ በመውሰድ ከደሙ ንጹህ ለመምሰል ሙከራዎች ሲያደርግ ይታያል። በኮሎራዶ የህወሃት አስተባባሪ የሆኑት  ወርቁ፣ ፈጸመ፣ ሰመረ፣ ወንዶሰን፣ ይሳቅ የጎንደር እና የደቡብ ልጆች ናቸው፤ ማለትም ታማኝ የህወሃት አገልጋዮች ሲሆኑ በየጊዜው በይፋ የህወሃት ስብሰባዎችን የሚያዘጋጁ ሲሆኑ እነዚህን ከበስተጀርባ ሆኖ የሚነዳቸው ግን የህወሃት አባል የትግራይ ተወላጆች ናቸው።

ይህ በንዲህ እንዳለ ነው ኮሎራዶ በተቃዋሚዎች ከፍተኛ ጥረት እና ትብብር የኮሎራዶ ኢትዮጵያውያን ነዋሪዎች ለሃገርና ለሕዝብ የቆሙ ግለሰቦችና ኢትዮጵያውያን ድርጅትና፤ ተቋማት የሚያደርጉት ያላሳለሰ የአንድነት ጥረት ይበረታታል። ይሁን እንጂ ከላይ እንደገለጽኩት በባንዳ ተላላኪ እና ለሆዳቸው ባደሩ ለማን እንደሚሰሩ በማያውቁ ሰዎች በመደገፍ ህወሃት/ወያኔ አሰልጥኖ ያሰማራቸው ቅጥረኞች ሕዝብን ሳይፈሩና ሳያፍሩ የባንዳነት ተግባራቸውን ቀጥለውበት ይገኛሉ።

ጥሩ ምሳሌ፡- በኮሚውኒቲ ደረጃ ሁለት አይነት ኮሚውኒቲ አለ። አንደኛው በግልጽ ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ሰበአዊ መብት የሚከራከር ከ20 አመት በላይ ያስቆጠረ በኢትዮጵያኖች እጅ ተይዞ የሚገኝ ሁሌም በሀገራዊ ጉዳዮች ያገባኛል የሚል ኮሚውኒቲ በአቶ ሽፈራው የሚመራ ሲሆን፤

ሌላኛው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባለመስማማት የተፈጠረ ነገር ግን የወያኔ ሰዎች የወረሩት እና ተቃዋሚዎችም የነበሩትና ግለሰቦች በጥቅማ ጥቅምና በፍርሃት አገልጋይ የሆኑበት በአቶ መለሰ ወርቅነህ የሚመራው ኮሚውኒቲ ነው።

የሁለቱ ኮሚውኒቲ ልዩነቶችና የሚመራው አካል፡-

በእነ አቶ ሽፈራው የሚመራው፡- የኢትዮጵያ ባንዲራ አርንጎዴ ቢጫ ቀይ ነው፣ የሰበአዊ መብት ጥሰቶች ካሉ በኮሚውኒቲያችን ላይ የደረሰ በደል ስለሆነ ማውገዝ ግዴታችን መሆን አለበት፣ ከመንግስት የሚደረጉ ድጋፎችን አንቀበልም፣ ለዝና ብለን አንሰራም የሚል ነው። እነ አቶ አስቻለው ከእኛ ተገንጥለው የወጡ ናቸው ህጋዊ ኮሚውኒቲ አይደሉም የአንድ መንግስት ደጋፊ ናቸው። ኢትዮጵያውያን በአርብ ሀገራት ለደረሰባቸው እንግልትና ሞት ተጠያቂው መንግስት አይደለም፣ መንግስትን አትቃወሙብን በማለት በአደባባይ በጠሩት ሰልፍ የወያኔን ባንዲራ ይዘው ማንነታቸውን ያስመሰከሩ ናቸው ይሁን እንጂ በአማካሪ ቦርድ ስም ደግሞ ‘ተቃዋሚ” ቢኖሩም ንጹህ በሚል ሽፋን ለወያኔ ጥቃት ተጋልጠናል የሚባሉ ግለሰቦች አሉበት የሚሉ ናቸው።

    በአቶ መለሰ (የህወሃት አባል እና የትግራያን ኮሚውኒቲ መስራች) ኦፊሻል ባንዲራችን በዩናይትድ ኔሽን የጸደቀው የኮኮብ ምልክት ያለበት ነው፣ (ይህ በዚህ ቡደን አማካሪ ቦርድ በሆኑት በእነ ፕ/ር ሚንጋ ተቃውሞ ውድቅ ተደርጎል) በኢትዮጵያ ሰበአዊ መብቶች ጉዳይ ላይ አያገባንም እኛ ውጪ ነን ያለነው፣ መንግስት የሚያወጣቸውን እንደ 40/60 ጥቅማጥቅሞች ለህዝብ ማድረስ ይገባናል፣ ያኛው ኮሚውኒቲ በኢሃፓ እና በግንቦት 7 የሚመራ ነው፣ እነ አቶ ሽፈራው ግትሮች ናቸው፣ ኮሚውኒቲውን እየከፋፈሉብን ነው የሚሉ የክስ መላምቶች አሉበት።

ድህረ ገጽ http://ethiopiancommunityofcolorado.org/announcment

በህወሃት ይመራል የሚባለውን ኮሚውኒቲ አመራሮችና እና ጀርባ ያሉ ግለሰቦችን ዝርዝር በሚቀጥለው ጽሁፌ ይዤ እወጣለሁ።

እንግዲህ በዚህ ፍትጊያ ህወሃት የሚሰራውን የውስጥ ስራ አጠናክሮ እየሰራ ነው። ተቃዋሚውን በመክፈል ተቃዋሚ የነበሩትን ገለልተኛ በማድረግ ከትግሉ እንዲወጡ እያደረገ ነው። ለዚህ ደግሞ በከፍተኛ ደረጃ በወያኔነት የማይጠረጠሩትን ግለሰቦች በመያዝ ክፍፍልን መፍጠር ሁነኛ ስራው አድርጎታል። ለዚህ ደግሞ ኮሎራዶ ምቹ ነች! የወያኔን ሞፈር መሸከም የሚችሉ ያሉባት፣ ዝና ፈላጊዎች የሚታዩባት፣ የኔ ሃሳብ ብቻ የሚል ያለባት፣ የህወሃት እህት ከተማ የሆነች ስትሆን በቀላሉ ባንዳዎችን በብልጭልጭ መፍጠር የሚቻልባት ውጣ ውረድ ያለባት ተራራማ ከተማ።

የኢሳት ኮሎራዶ ቻፕተር የዛሬ አመት ይህንኑ ኮሚውኒቲ እንዲረዳው በድበዳቤ ሲጠይቅ በእነ አቶ አስቻለው አማካኝነት ይህ የተቃዋሚ ድርጅት ሚዲያ ስለሆነ አንረዳም መተዳደሪያ ደንባችን ፓለቲካ ውስጥ እንደንገባ አይፈቅድም ሲሉ ምላሽ መስጠታቸው የሚታወስ ሲሆን፤ በአንጻሩ ደግሞ በእነ አቶ ሽፈራው የሚመራው ኮሚውኒቲ ለኢሳት በላከው ደብዳቤ ኢሳት የኢትዮጵያኖች CNN እንዲሆን ተመኝተው ነጻ የሚዲያ አውታር ሆኖ እንዲቀጥል መደገፍ አለበት በሚል ከገንዘብ እስከ ጊዜ መሰዋእት አደርገዋል። እዚህ ላይ ሳይጠቀሱ የማይታለፉ ጉዳይ ቢኖር የኢሳት ኮሎራዶ አስተባባሪ በወቅቱ ከፍተኛ በሆነ ሀገራዊ ሞራልና ብርታት ደከመኝ ሳይሉ ሁሉንም ወገኖች እንዲሳተፉ ያደረጉት ጥረት ይደነቃል።

በአሁኑ ሰአት ደግሞ ይሔው ኮሚውኒቲ በመከፋፈል ላይ ነው ቢባልም በእነ አቶ አስቻለው አማካኝነት ኮሚውኒቲውን ከፖለቲካ አናሰገባም፣ ይሁን እንጂ መንግስትን ግን እንደ አንድ ሀገር መንግስት በመንግስትነቱ እንቀበለዋለን። ተቃዋሚው እኮ ራሱ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አሳልፎ የሰጠው ግንቦት 7 ነው። ስለዚህ እኛን ለምን ፖለቲከኛ ሁኑ ትሉናላችሁ በሚል የካድሬ ቅስቀሳ እያደረጉ ይገኛሉ። እንግዲህ የሚባሉትን የሚናገሩ እንጂ ከእራሳቸው ጋር ኖረው የማያውቁ ጥርቅም ጉጅሌዎች ያሉበት ቡድን መሆኑን ለማየት ይህ በቂ ነው።

ዞሮ ዞሮ ኮሎራዶ ተቃዋሚው ሲጠነክር ወደ ተቃዋሚው የምታጋድል፤ ህወሃት ሲጠነክር ደግሞ ወደ ህወሃት የምትሄድ ከተማ ነችና የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡ ተኩላዎች በመጠንቀቅ ኮሚውኒቲው ለወያኔ አገልጋይና አደርባይ እንዳይሆን እነሱ በሚጠሩት ማናቸውም ስብሰባ ባለመገኘት ነዋሪው አንድነታችንን ማሳየትና መጠበቅ አለበት። በአለም አቀፍ ደረጃ የወያኔ ሰዎችን የሚተባበሩ፣ የጥቅሙ አገልጋዮች የሆኑትን ግለሰቦች፣ ድርጅቶች በየከተማችን በማውጣት ህወሃትን በተመባበራቸው የታሪክ ተጠያቂ እንደሆኑ መንገር ተገቢ ነው። በገለልተኛ ስም “ወይን ለኑሮ” ተቀባይነት የሌለው የኑሮ ዘይቤ መሆኑን በግልጽ ማሳየት ይኖርብናል። ዛሬ በወያኔ ወህኒ ቤቶች ተወርውረው የሚገኙት ሰመአታት ኮሚውኒቲው እንደሚለው ሳይሆን ለእናት ሀገራቸው ከበርሃ በርሃ ሲንከራተቱ መሰዋእት የሆኑ የቁርጥ ልጆች እንጂ፤ አእምሮ የሌላቸው ትንንሽ ሽፍን ሆዳሞች እንደሚሉት እንዳልሆነ የሚረዱበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።

ለዚህ ተምሳሌት ኦገስት 9 በኮሎራዶ እኔም አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ በሚል የተዘጋጀው ስብሰባ ማህበረሰቡ ያሳየው ድጋፍ የሚበረታታ ነው። ምናልባትም አንዳርጋቸው እሱ መሰዋእት ሆኖ ያስተሳሰረን ይመስላል።

በመጨረሻም የህወሃት አባላት የሆናችሁ በተለይም በኮሚውኒቲው ስም የምትገኙ ፡- አሁንም በኮሎራዶ የምታደርጉትን የድርጅት ድጋፍ እስከአላቆማችሁ ድረስ የምታደርጉትን እየተከታተልን ለህዝብ የምናሳወቅ መሆኑን እንገልጻለን።

ጨረስኩ

ያላችሁን አስተያየት በ loveethio777@gmail.com ይላኩልኝ

የዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የአፍ ወለምታ (ኤፍሬም ማዴቦ)

August 20/2014
የዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የአፍ ወለምታ (ኤፍሬም ማዴቦ)
የዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የአፍ ወለምታ (ኤፍሬም ማዴቦ)
ባለፈዉ ሰሞን ቻይና አፍሪካ ዉስጥ ሰላሳ አመት በማይሞላ ግዜ ዉስጥ ያደረገችዉ የኤኮኖሚና የፖለቲካ መስፋፋት ያሳሰባቸዉ የአሜሪካዉ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ምነዉ ምን አድረግናችሁና ነዉ ፊታችሁን ያዞራችሁብን ብለዉ ለመጠየቅ በርከት ያሉ የአፍሪካ መሪዎችን ቤተ መንግስታቸዉ ድረስ ጋብዘዋቸዉ ነበር። በዚህ የሃሳብ ልዉዉጥ፤ ምክር፤ የእራት ግብዣና የዋሺንግተን ዲሲን ጉብኝት ባጠቃለለዉ የፕሬዚዳንት ኦባማ ድግስ ላይ በመልካም የዲሞክራሲ ጅምራቸዉ የሚወደሱት የጋናና የደቡብ አፍሪካን መሪዎች ጨምሮ እንመራሀለን የሚሉትን ህዝብ በየቀኑ የሚያስሩት፤ የሚደበድቡትና የሚገድሉት የወያኔ መሪዎችም ተገኝተዋል። በዚህ የመሪዎች ስብሰባ ላይ ጠ/ሚ ደሳለኝ ኃ/ማሪያምን አጅበዉ ከመጡት የወያኔ ሹማምንት አንዱ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ./ር ቴድሮስ አድሃኖም ነበሩ። ዶ/ር ቴድሮስ በዋሽንግተን ዲሲ ቆይታቸዉ ብዙዎቻችንን እየዋለ ሲያድር ደግሞ እራሳቸዉንም ግራ ያጋባ የሬድዮ ቃለ መጠይቅ ሰጥተዉ ነበር።
“በአፍ ይጠፉ በለፈለፉ” የአገራችን ባለቅኔዎች አፉ እንዳመጣለትና እንዳሻዉ የሚናገርን ሰዉ . . .  ዋ ተጠንቀቅ በአፍ የሚነገር ነገር ዋጋ ያስከፍላል ለማለት የተረቱት ተረት ነዉ።  አዎ! ባለቅኔዎቹ እዉነታቸዉን ነዉ።  የሚያዳምጡንን ሰዎች ለማስደሰት ስንል ብቻ አፋችን እንዳመጣ የባጥ የቆጡን የምንዘባርቅ ሰዎች የምንላቸዉ ነገሮች እኛዉ ዘንድ ዞረዉ መጥተዉ መጥፊያችን ሊሆኑ ይችላሉ። በቅርቡ ዋሺንግተን ዲሲ ብቅ ብለዉ የነበሩትን የኢትዮጵያ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖምን ያጋጠማቸዉ ይሄዉ በጋዛ አፍ ተናግሮ የመጥፋት ቅሌት ነበር። ዶ/ር ቴድሮስ እዚህ ዋሽንግተን ዲሲ ዉስጥ መንግስታቸዉ የሰራተኛ ደሞዝና የአየር ላይ ወጪ እየከፈለ በሚያስተዳድረዉ ሬድዮ አፋቸዉን ሞልተዉ የተናገሩትን ነገር አዲስ አበባ ተመልሰዉ በፌስ ቡካቸዉ በለቀቁት መልዕክት ለማስተባበል ቢሞክሩም ነገሩ “ከአፍ ከወጣ አፋፍ” ሆኖባቸዉ በስህተት ላይ ስህተት እየፈጸሙ ይገኛሉ።
ሬድዮ አገር ፍቅር በመባል ከሚታወቀዉ ሳምንታዊ ሬድዮ ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በእስር ላይ የሚገኙት የድምጻችን ይሰማ መሪዎች የአሜሪካ መንግስት ጓንታናሞ ዉስጥ ካሰራቸዉ የአልቃይዳ አባላት ጋር ግንኙነት እንዳላቸዉ ማረጋገጫ አግኝተናል ካሉ በኋላ የአሜሪካ መንግስት ይህንን ግኑኝነት አስመልክቶ የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን ኢትዮጵያ ድረስ ሄዶ ለማነጋገር ለመንግስታቸዉ ጥያቄ እንዳቀረበ ተናግረዋል። ያልነገሩን ነገር ቢኖር የአሜሪካ መንግስት ባቀረበዉ ጥያቄ መሰረት ቃሊቲ ድረስ ሄዶ የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን ማነጋገሩንና አለማነጋገሩን ብቻ ነዉ።
ዶ/ር ቴዎድሮስ ብቻ ሳይሆኑ እሳቸዉ በአባልነት የሚገኙበት ህወሃት የሚባዉ ድርጅት ሃያ ሦስት አመት ሙሉ እየዋሸ የዘለቀ ድርጅት ነዉና የዶ/ር ቴድሮስ ዉሸት ብዙም ላይገርመን ይችላል። ሆኖም ግን ዶ/ር ቴድሮስ ግማሽ ደቂቃ በማይሞላ ግዜ ዉስጥ ሁለት ቱባ ቱባ ዉሸቶችን ሲዋሹ “ከማንም ጋር አንወግንም፤ የቆምነዉ ለእዉነት ብቻ ነዉ” የሚለዉ የአገር ፍቅር ሬድዮ ጣቢያ አዘጋጅ ካለምንም ተከታይ የማብራሪያ ጥያቄ የዶ/ር ቴድሮስን ቆሞ የሚሄድ ዉሸት እንዳለ ተቀብሎ ጭራሽ ዶ/ር ቴድሮስን ማመስገኑ የወያኔ ስርዐት ዉሸትና ቅጥፈት አገር ዉስጥ ብቻ ሳይሆን በዉጭ አገሮችም ምን ያክል ህብረተሰባችንን አንደበከለ ያሳያል።
የኢትዮጵያን የእስልምና እምነት ተከታዮች ከአልቃይዳ ጋር ማገናኘት እነዚህ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ያነሱትን ህጋዊ የመብትና የነጻነት ጥያቄ ላለመመለስ የሚደረግ አጉል ዉጣ ዉረድ ከመሆኑ አልፎ ማንም ማየትና ማሰብ የሚችል ሰዉ የማይቀበለዉ ከንቱ ቅጥፈት ነዉ። ደግሞም ይብላኝ ለዶ/ር ቴድሮስ አፋቸዉን ላዳለጣቸዉ እንጂ ወጣቶቹ የድምጻችን ይሰማ መሪዎችኮ የጓንታናሞ አስር ቤት ሲከፈት ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት መፍጠር ቀርቶ አልቃይዳ የሚባል ነገር መኖሩን እንኳን ሰምተዉ የማያዉቁ አንድ ፍሬ ልጆች ነበሩ።
ሌላዉ የዶ/ር ቴድሮስ ትልቁ ዉሸት የአሜሪካ መንግስት ከአልቃይዳ ጋር  የነበራቸዉን ግንኙነት አስመልክቶ የድምጻችን ይሰማ መሪዎችን የታሰሩበት ቦታ ድረስ ሄዶ ላናግራቸዉ ብሎ ጠየቀን ማለታቸዉ ነዉ። እኔ እንደሚመስለኝ ዶ/ር ቴድሮስ አደስ አበባ ከገቡ በኋላ “ምን ነካኝ” ብለዉ ዉሸታቸዉን በፌስ ቡክ ገጻቸዉ ለማስተባበል የቸኮሉት ደጋግመዉ ወዳጃችን ነዉ ብለዉ በተናገሩት በአሜሪካ መንግስት ስም የዋሹት ዉሸት ከንክኗቸዉ ይመስለኛል፤ አለዚያማ ወያኔም ሆነ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ዶ/ር ቴድሮስ በዋሹ ቁጥር ዉሸታቸዉን የሚያስተባብሉ ቢሆን ኖሮ የወያኔ አገዛዝ መሪዎች ስራቸዉ እየዋሹ ማስተባበል ብቻ ይሆን ነበር።
የሚገርመዉ ዶ/ር ቴድሮስ ከአሜሪካ ተመልሰዉ አዲስ አበባ ከገቡ በኋላ የመጀመሪያዉን አንድ ሳምንት ያሳለፉት አንድም አሜሪካ ዉስጥ የዋሹትን ዉሸት በማስተባበል ሌላ ግዜ ደግሞ ሌሎች አዳዲስ ዉሸቶችን በመዋሸት ነበር። በእርግጥም ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በየአገሩ የሚገኙትን አምባሳደሮቻቸዉን ሰብስበዉ የኢትዮጵያን ህዝብ ከት አድርጎ ያሳቀ ነጭ ዉሸት ዋሽተዋል። ለምሳሌ አሜሪካ ዉስጥ የህዳሴዉ ግድብ ቦንድ ሽያጭ እጅግ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ከተናገሩ በኋላ ምክንያቱን ሲገልጹ የአሜሪካ ህግ ለቦንድ ሽያጩ አመቺ አለመሆኑን ገልጸዉ ይህንን ለማሻሻል መንግስታቸዉ ከአሜሪካ መንግስት ጋር አብሮ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። መቼም ለራሱ አገር ይህ ነዉ ተብሎ ሊጠቀስ የሚችል ህግ አዉጥቶ የማያወቀዉ እንቅልፋሙ የኢትዮጵያ ፓርላማ የአሜሪካንን መንግስት የሚገዛ ህግ ካላወጣ በቀር ዶ/ር ቴድሮስ አደራ የተጣለባቸዉን የቦንድ ሽያጭ እንዴት አሜሪካ ዉስጥ እንደሚወጡት ባላዉቅም መንግስታቸዉ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ባለበት ቦታ ሁሉ ሁሉ ቦንድ መሸጥ ያልቸለዉ የየአገሮቹ ህግ ችግር ፈጥሮበት ሳይሆን ለወገኖቹ መብትና ነጻነት የሚታገለዉ ኢትዮጵያዊ ወንድሞቼንና እህቶቼን እየገደላችሁ የምትሸጡልኝ ቦንድ ባፍንጫዬ ይዉጣ ብሎ እምቢ ስላላቸዉ ነዉ። ይህንን ደግሞ መዋሸት እንጂ እዉነትን ሸፍኖ ማስቀረት ያልቻሉት ዶ/ር ቴድሮስም ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ በስተቀር የሁሉም አገሮች የቦንድ ሽያጭ እጅግ በጣም ደካማ እንደነበር ለሰበሰቧቸዉ አምባሳደሮች ተናግረዋል፡፡
ከዶ/ር ቴድሮስ በፊትም ሆነ እሳቸዉ እያሉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከትዉልድ አገሩ ርቆ የሚኖረዉን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ በጥቅማ ጥቅም እየደለለ ከአገዛዙ ጎን ለማሰለፍ ተደጋጋሚ ጥረቶችን አድርጓል። በተለይ የህዳሴዉን ግድብ ቦንድ ሽያጭና  የዕድገትና ትራንስፎርሜሺኑን ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግ የወያኔ/ኢህአዴግ አገዛዝ ዳያስፖራዉን አንደ ከፍተኛ የዉጭ ምንዛሬ ምንጭ ተመልክቶት ነበር፤ ሆኖም አብዛኛዉ ዳያስፖራ ከአገዛዙ ጎን ተሰልፎ ከሚያገኘዉ ግዜያዊ ጥቅም ይልቅ ዘላቂ የሆነዉን የእናት አገሩን አንድነትና የወገኖቹን ፍትህ፤ ነጻነትና እኩልነት በመምረጡ የወያኔ/ኢህአዴግ አገዛዝ ከዳያስፖራዉ እዝቃለሁ ብሎ የተመኘዉ የዉጭ ምንዛሬ ህልም ሆኖ ቀርቷል።
ሌላዉ የወያኔ/ኢህአዴግ አገዛዝ ከፍተኛ በጀትና የሰዉ ኃይል መድቦ ዳያስፖራዉን ለማማለል በሙሉ ሀይሉ የተንቀሳቀሰበት አካባቢ ቢኖር የከተማ ቦታና ቤት ሽያጭ ዘመቻ ነዉ። በእርግጥ አንዳንድ ከህዝብና ከአገር ጥቅም ይልቅ የራሳቸዉን ጥቅም ያስቀደሙ የዳያስፖራዉ አባላት ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚካሄደዉን የመሬት ቅርምት በይፋ እየተቃወሙ የቅርምቱ ድግስ የእነሱን ቤት ሲያንኳኳ ግን በራቸዉን ወለል አድርገዉ ከፍተዉ የድግሱ ተሳታፊዎች ሆነዋል። አብዛኛዉ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ግን እናትና አባቴን እያፈናቀላችሁ የምትሰጡኝን መሬትም ሆነ ቤት አልፈልግም ብሎ በቦንድ ሽያጩ ላይ የወሰደዉን ጠንካራ አቋም በከተማ መሬትና ቤት ሽያጭ ላይም ደግሞታል። የወገኖቹን ነጻነትና ፍትህ ለማስከበር በህይወቱ የተወራረደዉን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ የማያወላዉል አቋም ያልተረዱት ዶ/ር ቴድሮስ ግን ያንን የለመዱትን በጥቅማ ጥቅም የመደለል ሴራቸዉን አሁንም እንደቀጠሉበት ነዉ። ለምሳሌ ዳያስፖራዉ በመጪዉ አመት በሚደረገዉ የምርጫ ድራማ ላይ ያለዉን እይታ እንዲለዉጥ ለማድረግ ሲባል ብቻ 40 በ60 በሚባለው የቤቶች መርሃግብር የታቀፉ የዲያስፖራ አባላት የከፈሉበት ቤት የ2007ቱ ምርጫ ከመጀመሩ በፊት በአስቸኳይ ተጠናቅቆ እንዲሰጣቸዉ ትዕዛዝ ተላልፏል። እዚህ ላይ አንድ እጅግ በጣም የገረመኝም ያሳዘነኝም ነገር ቢኖር በአንድ በኩል ግብር ከፋይ በሌላ በኩል ደግሞ ቤት አልባ የሆነዉና እነ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም 99.6% መረጠን የሚሉት አገር ዉስጥ የሚኖረዉ ኢትዮጵያዊ ተረስቶ ትርፍ ቤት ፈላጊዉ ዳያስፖራ ቅድሚያ እንዲሰጠዉ መደረጉ ነዉ።
ለመሆኑ ዶ/ር ቴድሮስና መንግስታቸዉ ሁሌም አክራሪዉ ዳያስፖራ እያሉ የሚያሙትን ማህበረስብ ወድደዉ ሊስሙት ነዉ ወይን ተጠግተዉ ሊያልቡት እንዲህ የተንሰፈሰፉለት? የዳያስፖራዉን አባት፤ እናት፤ ወንድምና እህት እያሰሩ፤ እየገደሉና የመብትና የነጻነት ጥያቄ የሚያነሳባቸዉን የዳያስፖራ አባል ደግሞ አገርህ አትገባም ብለዉ አገር እየነሱት እነሱ ግን የልመና ኮሮጇቸዉን ተሽክመዉ አሜሪካና አዉሮፓ እየመጡ አገርህን እናሳድግልሃለን ገንዘብ ስጠን ብለዉ የሚጠይቁት በማን አገር ማን ለሚጠቀምበት ልማት ነዉ? እነ ዶ/ር ቴድሮስ እነሱን ከመሰለ ፀረ ህዝብ አገዛዝ ጋር ተመሳጥረዉ የዳያስፖራዉን አባል በህገ ወጥ መንገድ አግተዉ እየደበደቡና መታሰሩን ሰምታ ልትጠይቀዉ የሄደችዉን እህቱን ተወልዳ ካደገችበትና እትብቷ ከተቀበረበት አገር በ24 ሰዐት ዉስጥ ዉጪ ብለዉ እያስገደዱ እንዴት ቢገምቱንና እንዴት ቢመለከቱን ነዉ ዞር ብለዉ እኛኑ ገንዘብ ስጡን ብለዉ የሚጠይቁን?
ዶ/ር ቴድሮስ ከአገር ፍቅር ሬድዮ ጋር ያደረጉትን ቃለ መጠይቅ ከማጠቃለላቸዉ በፊት ደጋግመዉ የተናገሩት ኢትዮጵያን ምን ያክል እንደሚወዱና ይህ የሚወዱት አገር ህዝብ በእድገት ወደ ፊት ከገፉ አገሮች ተርታ ተሰልፎ ማየት አንደሚቸኩሉ ነዉ። መልካም ምኞት ነዉ። ሆኖም ይህ ምኞት የዚያችን የሚወዷትን አገር ህዝብ ሲናገር አፉን እየዘጉ፤ ሲጽፍ እጁን እያሰሩ፤ ሃሳቡን ሲገልጽ ማዕከላዊ ወስደዉ ሰቅለዉ እየገረፉና  ሰላማዊ ሠልፍ ተሰልፎ መብቴንና ነጻነቴን አክብሩልኝ ብሎ የጠየቃቸዉን ደግሞ ደረቱንና ጭንቅላቱን በጥይት እያፈረሱ የሚሳካ ምኞት አይደለም።  ዶ/ር ቴድሮስ በአፋቸዉ ብቻ የሚናገሩት ምኞት ዳያስፖራዉ በአፉም በልቡም ዉስጥ ያለ፤ የነበረና ለወደፊትም የሚኖር ምኞት ነዉ። ምኞታችንና ምኞታቸዉ ገጥሞ ኢትዮጵያ አድጋና በልጽጋ የምናያት  ግን ዶ/ር ቴድሮስ  እኛም እንደሳቸዉ በአገራችን ጉዳይ እንደሚያገባን በዉል ሲረዱና ይህንን ሃያ ሦስት አመት ሙሉ በችንካር ቀርቅረዉ የዘጉብንን በር ወለል አድርገዉ ሲከፍቱ ብቻ ነዉ።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በልጆቿ መስዋዕትነት ይረጋገጣል!!!!