Monday, April 28, 2014

የሰማያዊ ፓርቲ አባል ፈተና እንዳይፈተን ተከለከለ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ አመት የምህንድስና ተማሪ የሆነው ዮናስ ከድር ሰማያዊ ፓርቲ ለጠራው ሰልፍ ሲቀሰቅስ ተይዞ ጉለሌ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ ይገኛል፡፡ እስር ቤት ውስጥ ያለ ተማሪ በፖሊስ ታጅቦ ፈተናውን የመፈተን መብት ቢኖረውም ዮናስን ግን ‹‹አንተ የፖለቲካ እስረኛ ነህ፣ አንተን አጅበን ማስፈተን አንችልም፣ አንተን የሚያጅብ ፖሊስ የለንም!›› የሚሉ የተለያዩ ምክንያችን በመደርደር ለፈተና እንዳይቀርብ ተደርጓል፡፡10330474_10152416602689743_8094249108584679939_n

No comments:

Post a Comment